-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
ሁለቱ ምሥክሮች ተገደሉ
19. የራእይ መጽሐፍ በሚሰጠው መግለጫ መሠረት ሁለቱ ምሥክሮች የምሥክርነት ሥራቸውን ሲፈጽሙ ምን ይሆናል?
19 ይህ በሕዝበ ክርስትና ላይ የወረደው መቅሰፍት በጣም ከባድ ስለነበረ ሁለቱ ምሥክሮች ለ42 ወራት ማቅ ለብሰው ከመሰከሩ በኋላ ሕዝበ ክርስትና ባላት ዓለማዊ ተደማጭነት ተጠቅማ ‘አስገደለቻቸው።’ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ጽፎአል:- “ምስክራቸውን ከፈጸሙ በኋላ ከጥልቁ የሚወጣው አውሬ ይዋጋቸዋል ያሸንፋቸውማል ይገድላቸውማል። በድናቸውም በታላቂቱ ከተማ አደባባይ ይተኛል እርስዋም በመንፈሳዊ ምሳሌ ሰዶምና ግብጽ የተባለች ደግሞ ጌታቸው የተሰቀለባት ናት። ከወገኖችና ከነገዶችም ከቋንቋዎችም ከአሕዛብም የሆኑ ሰዎች ሦስት ቀን ተኩል በድናቸውን ይመለከታሉ፣ በድናቸውም ወደ መቃብር ሊገባ አይፈቅዱም። እነዚህም ሁለት ነቢያት በምድር የሚኖሩትን ስለ ሣቀዩ በምድር የሚኖሩት በእነርሱ ላይ ደስ ይላቸዋል በደስታም ይኖራሉ እርስ በርሳቸውም ስጦታ ይሰጣጣሉ።”— ራእይ 11:7-10
20. “ከጥልቁ የሚወጣው አውሬ” ምንድን ነው?
20 ‘አውሬ’ የሚለው ቃል በራእይ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሰው 37 ጊዜ ሲሆን ይህ የመጀመሪያው ጊዜ መሆኑ ነው። ስለዚህኛውም ሆነ ስለተቀሩት ሌሎች አውሬዎች ቆየት ብለን እንመረምራለን። ለአሁኑ ግን “ከጥልቁ የወጣው አውሬ” ሰይጣን የፈጠረው ሕያው የፖለቲካ ሥርዓት ነው ማለት ብቻ ይበቃናል።b—ከራእይ 13:1ና ከዳንኤል 7:2, 3, 17 ጋር አወዳድር።
21. (ሀ) የሁለቱ ምሥክሮች ሃይማኖታዊ ጠላቶች ጦርነቱ በፈጠረው ሁኔታ የተጠቀሙት እንዴት ነው? (ለ) የሁለቱ ምሥክሮች አስከሬን ሳይቀበር መቅረቱ ምን ያመለክታል? (ሐ) የሦስት ቀን ተኩሉን የጊዜ ርዝመት እንዴት መረዳት ይኖርብናል? (የግርጌ ማስታወሻ ተመልከት።)
21 ከ1914 እስከ 1918 ድረስ በነበረው ጊዜ ብሔራት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ተወጥረው ነበር። የብሔረተኝነት ስሜት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ጊዜ ነበር። በ1918 የጸደይ ወራት የሁለቱ ምሥክሮች ሃይማኖታዊ ጠላቶች በተፈጠረው ሁኔታ ለመጠቀም ተነሱ። የመንግሥታትን ሕጋዊ መሣሪያዎች በመጠቀም ከመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎቹ መካከል በኃላፊነት የሚሰሩ አገልጋዮችን በሐገር ክህደት የሐሰት ክስ አስወንጅለው አሳሰሩ። በታማኝነት ይተባበሩአቸው የነበሩ ባልደረቦቻቸው በነገሩ ተደናገጡ። የመንግሥቱ ሥራ የቆመ ያህል መሰለ። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመናት በመታሰቢያ መቃብር ውስጥ አለመቀበርና በውጭ መጣል ትልቅ ውርደት ነበር። (መዝሙር 79:1-3፤ 1 ነገሥት 13:21, 22) ስለዚህ ሁለቱ ምሥክሮች አለመቀበራቸው ትልቅ ውርደት እንደሚደርስባቸው ያመለክታል። በጣም ሞቃት በሆነው የፓለስጢና አየር ጠባይ በመንገድ ላይ የተጣለ አስከሬን ከሦስት ቀን ተኩል በኋላ መሽተት ይጀምራል።c (ከዮሐንስ 11:39 ጋር አወዳድር።) እነዚህ በትንቢቱ ውስጥ የተነገሩት ዝርዝር ጉዳዮች ሁለቱ ምሥክሮች የሚደረስባቸውን ከፍተኛ ውርደት ያመለክታሉ። ከላይ የጠቀስናቸው አገልጋዮች ጉዳያቸው በይግባኝ በሚታይበት ጊዜ እንኳን የዋስ መብት ተነፍጎአቸው ነበር። “በታላቂቱ ከተማ” ለሚኖሩት ሰዎች እስኪሸቱ ድረስ በአደባባይ ተጋልጠዋል። ይሁን እንጂ ይህች “ታላቅ ከተማ” ማን ነች?
22. (ሀ) ታላቂቱ ከተማ ምንድን ነች? (ለ) ሁለቱ ምሥክሮች ፀጥ እንዲሉ በመደረጋቸው የሕዝብ ጋዜጦች ከቀሳውስት ጋር በመተባበር ደስ መሰኘታቸውን የገለጹት እንዴት ነው? (ሣጥኑን ተመልከት።)
22 ዮሐንስ አንዳንድ ፍንጭ ሰጥቶናል። ኢየሱስ በዚህች ከተማ እንደተሰቀለ ተናግሮአል። ይህን ሲለን ወዲያውኑ ወደ አእምሮአችን የምትመጣው ከተማ ኢየሩሳሌም ነች። በተጨማሪም ታላቂቱ ከተማ ሰዶምና ግብጽ ተብላ እንደምትጠራ ተናግሮአል። የጥንትዋ ኢየሩሳሌም በመጥፎ ድርጊቶችዋ ምክንያት ሰዶም ተብላ የተጠራችበት ጊዜ ነበር። (ኢሳይያስ 1:8-10፤ ከሕዝቅኤል 16:49, 53-58 ጋር አወዳድር።) ከዚህም በላይ የመጀመሪያዋ የዓለም ኃያል መንግሥት የነበረችው ግብጽ የዚህ ዓለማዊ ሥርዓት ምሳሌ የሆነችባቸው ጊዜያት አሉ። (ኢሳይያስ 19:1, 19፤ ኢዩኤል 3:19) ስለዚህ ይህች ታላቅ ከተማ አምላክን አመልካለሁ እያለች እንደ ሰዶም በአምላክ ፊት እርኩስና ኃጢአተኛ ሆና የተገኘችውን “ኢየሩሳሌም” ታመለክታለች። የከሃዲዋ ኢየሩሳሌም ዘመናዊ እኩያ የሆነችው የሕዝበ ክርስትና ምሳሌ ነች። የሕዝበ ክርስትና አባሎች ሰላም ያሳጣቸውን የሁለቱን ምሥክሮች ስብከት ጸጥ ለማሰኘት በመቻላቸው በጣም ተደስተዋል።
-
-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
c በዚህ ጊዜ የአምላክ ሕዝቦች ያጋጠማቸውን ተሞክሮ በምንመረምርበት ጊዜ 42ቱ ወራት ቃል በቃል የሦስት ዓመት ተኩል ጊዜ የሚያመለክቱ እንደሆኑ ብንገነዘብም ሦስት ቀን ተኩሉ ግን ቃል በቃል የ84 ሰዓት ጊዜ አያመለክትም። የሦስት ቀን ተኩል ጊዜ ሁለት ጊዜ የተጠቀሰው (ቁጥር 9 እና 11 ላይ) ከዚያ በፊት ከነበረው የሦስት ዓመት ጊዜ ጋር ሲወዳደር አጭር ጊዜ እንደሚሆን ለማመልከት ይመስላል።
-