-
ማስታወቂያዎችየመንግሥት አገልግሎት—2006 | ሚያዝያ
-
-
ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች ሚያዝያና ግንቦት:- መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶች። ተመላልሶ መጠየቅ በምታደርጉበት ወቅት ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? የተባለውን መጽሐፍ አበርክቱ። ሰኔ:- ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው? ሐምሌ:- ብሮሹሮች።
◼ ለአውራጃ ስብሰባ ደረት ላይ የሚለጠፈው ባጅ ካርድ ከጽሑፎች ጋር ስለሚላክላችሁ ማዘዝ አያስፈልጋችሁም። ይሁን እንጂ ጉባኤው ተጨማሪ ካርድ ካስፈለገው በጽሑፍ ማዘዣ ቅጽ (S-14) ማዘዝ ይኖርበታል። በጉባኤያችሁ ውስጥ የባጅ መያዣ ፕላስቲክ የሚፈልጉ ካሉ ማዘዝ ይኖርባችኋል።
◼ የጉባኤ ጸሐፊዎች የዘወትር አቅኚነት አገልግሎት ማመልከቻ ቅጽ (S-205) እና የረዳት አቅኚነት አገልግሎት ማመልከቻ ቅጽ (S-205b) በበቂ መጠን ሊኖራቸው ይገባል። እነዚህ ቅጾች እንዲላኩላችሁ በጽሑፍ ማዘዣ ቅጽ (S-14) መጠየቅ ይቻላል። ቢያንስ ለአንድ ዓመት የሚበቁ ቅጾች ይኑሯችሁ። የዘወትር አቅኚነት ማመልከቻ ቅጾችን ወደ ቅርንጫፍ ቢሮው ከመላካችሁ በፊት በደንብ መሞላታቸውን ማረጋገጥ አለባችሁ።
◼ ቅርንጫፍ ቢሮው የሁሉንም ሰብሳቢ የበላይ ተመልካቾችና ጸሐፊዎች ወቅታዊ አድራሻና ስልክ ቁጥር ማግኘት ይፈልጋል። የአድራሻ ለውጥ በሚኖርበት ጊዜ የጉባኤው የአገልግሎት ኮሚቴ የሰብሳቢ የበላይ ተመልካች/የጸሐፊ የአድራሻ ለውጥ ማሳወቂያ ቅጽ (S-29) ሞልቶና ፈርሞ በፍጥነት ለቅርንጫፍ ቢሮው መላክ አለበት። የስልክ ቁጥር ለውጥ ሲኖርም እንደዚህ መደረግ ይኖርበታል።
◼ ታኅሣሥ 13, 2005 በላክንላችሁ ደብዳቤ ላይ የኦሮምኛ መጠበቂያ ግንብ ከጥናት ርዕሶች ሌላ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮችን አካትቶ እንደሚወጣ ገልጸንላችሁ ነበር። ለጊዜው ግን በወሩ ውስጥ የሚጠኑ የጥናት ርዕሶችን ብቻ ይዞ እንደሚወጣ ልንገልጽላችሁ እንወዳለን። በዚህ ቋንቋ የተዘጋጀውን መጽሔት ማግኘት የምትፈልጉ ሁሉ በጉባኤያችሁ በኩል ማዘዝ ትችላላችሁ።
◼ አዲስ የደረሱን ጽሑፎች:- አማርኛ፣ አረብኛ፣ ቻይንኛ፣ እንግሊዝኛ፣ ሂንዲ፣ ኑዌር፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ:- የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፤ ቻይንኛ:- T-75 (መከራና ሥቃይ ሁሉ በቅርቡ ይወገዳል!)፤ እንግሊዝኛ:- በሲዲ የተዘጋጀ የ2005 የመጠበቂያ ግንብ ቤተ መጻሕፍት፤ ኦሮምኛ:- አምላክ ስለ እኛ በእርግጥ ያስባልን?፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ፤ ሲዳምኛ:- T-26 (ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ይበልጥ ማወቅ ትፈልጋለህ?)፤ ትግርኛ:- ከታላቁ አስተማሪ ተማሩ፣ የይሖዋ ምሥክሮች እነማን ናቸው?፣ ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው 2006።
◼ በድጋሚ የደረሱን ጽሑፎች:- አማርኛ:- T-15 (አዲስ ዓለም)፣ T-19 (ይህ ዓለም ከጥፋት ይተርፍ ይሆን?)፣ T-26 (ስለ
-
-
“መዳናችን ቀርቧል!” የተባለውን የአውራጃ ስብሰባየመንግሥት አገልግሎት—2006 | ሚያዝያ
-
-
“መዳናችን ቀርቧል!” የተባለውን የአውራጃ ስብሰባ
ለማስተዋወቅ የሚደረግ ዓለም አቀፍ ዘመቻ በሁሉም ጉባኤዎች የሚገኙ አስፋፊዎች ልዩ የመጋበዣ ወረቀት ያሰራጫሉ
1 በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ በ2006 የጸደይ ወራት የሚጀምረው የአውራጃ ስብሰባ በመላው ዓለም በተከታታይ ይካሄዳል። አንድ መቶ ሃምሳ አምስት በሚያህሉ አገሮች የሚካሄደውን ይህን የአውራጃ ስብሰባ ለማስተዋወቅ ዓለም አቀፍ ዘመቻ ይደረጋል። ዘመቻው፣ ከሐምሌ አንስቶ እስከ ነሐሴ 2006 የመጀመሪያ ሳምንት ድረስ በጀርመን፣ በቼክ ሪፑብሊክና በፖላንድ የሚደረጉ ልዩ የአውራጃ ስብሰባዎችን ማስተዋወቅንም ይጨምራል።
2 የምንኖረው በመጨረሻዎቹ ቀናት ማብቂያ ላይ እንደመሆኑ መጠን አምላክ ሰዎችን ከዚህ ክፉ ዓለም ለማዳን የሰጠውን ተስፋ ጎላ አድርገው የሚገልጹት እነዚህ ስብሰባዎች ለዘላለም ሕይወት የተዘጋጁ ሰዎችን በእጅጉ እንደሚማርኳቸው እሙን ነው። የስብሰባው መልእክት ሰዎች ስለ ወደፊቱ ጊዜ እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል። ይህን አጽናኝና ተስፋ ሰጪ መልእክት ብዙ ሰዎች እንዲሰሙ ለማድረግ ሲባል ከ98,000 በላይ በሆኑ ጉባኤዎች ውስጥ የሚገኙ የይሖዋ ምሥክሮች ስብሰባውን በማስተዋወቁ ዘመቻ ላይ በቅንዓት ይካፈላሉ።
3 እያንዳንዱ አስፋፊ 50 የመጋበዣ ወረቀቶችን ማሰራጨት ይችል ዘንድ በቂ መጠን ያለው መጋበዣ ወረቀት ለየጉባኤው ይላካል። የተቀረውን መጋበዣ ወረቀት አቅኚዎች እንዲያሰራጩ ይደረጋል። እያንዳንዱ ጉባኤ የተመደበበት የአውራጃ ስብሰባ ከመደረጉ ከሦስት ሳምንት ቀደም ብሎ ዘመቻውን ይጀምራል። ይህም ሙሉ በሙሉ ባይሆንም እንኳ የጉባኤውን አብዛኛውን ክልል ለማዳረስ የሚያስችል በቂ ጊዜ እንዲኖር ያደርጋል።
4 የሚቻል ከሆነ የመጋበዣውን ወረቀት ለእያንዳንዱ የቤት ባለቤት መስጠት ጥሩ ነው። ሆኖም ሰዎቹ ቤታቸው የማይገኙ ከሆነ ጥበብ በተሞላበት መንገድ የመጋበዣውን ወረቀት በራቸው ላይ ትተንላቸው መሄድ እንችላለን። ሁሉንም መጋበዣ ወረቀቶች በሦስት ሳምንት ውስጥ አሰራጭቶ ለመጨረስ ትጋት የተሞላበት ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል።
5 ቀደም ሲል እንደተገለጸው፣ “መዳናችን ቀርቧል!” የተሰኘውን የአውራጃ ስብሰባ ለማስተዋወቅ በዓለም ዙሪያ የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ምሥክርነት ለመስጠት እንደሚያስችል እንተማመናለን። በመላው ዓለም በሚደረገው በዚህ ዘመቻ ላይ ለመካፈል የምታደርጉትን ጥረት ይሖዋ አብዝቶ እንዲባርከው ጸሎታችን ነው።
-