-
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳየመንግሥት አገልግሎት—2006 | ሚያዝያ
-
-
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳ
ሚያዝያ 24, 2006 በሚጀምር ሳምንት በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ላይ በቃል መልስ የሚሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚከተሉት ናቸው። የትምህርት ቤቱ የበላይ ተመልካች ከመጋቢት 6 እስከ ሚያዝያ 24, 2006 ባሉት ሳምንታት ውስጥ በቀረቡት ክፍሎች ላይ የተመሠረተ የ30 ደቂቃ ክለሳ ይመራል። [ማሳሰቢያ:- ከጥያቄው ቀጥሎ መልሱ የሚገኝበት ጽሑፍ ካልተጠቀሰ መልሱን ለማግኘት በግልህ ምርምር ማድረግ ይኖርብሃል።—የአገልግሎት ትምህርት ቤት ገጽ 36-7ን ተመልከት።]
የንግግር ባሕርይ
1. በምናስተምርበት ወቅት ከአንዱ ሐሳብ ወደ ሌላው ስንሸጋገር ቆም ማለት የሚያስፈልገን ለምንድን ነው? ሆኖም ይህን እንዳናደርግ ምን ሊያግደን ይችላል? [be ገጽ 98 አን. 3-4]
2. ለሌሎች ሰዎች ስንመሠክር በንግግራችን መሃል ቆም ማለት የሚያስፈልገን ለምንድን ነው? [be ገጽ 99 አን. 5 እስከ ገጽ 100 አን. 3]
3. ንግግር በምንሰጥበት ጊዜ ቁልፍ ቃላትን በተገቢው ሁኔታ ማጥበቅ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ይህንንስ ችሎታ እንዴት ልናዳብረው እንችላለን? [be ገጽ 101 አን. 1-5፣ ሣጥን]
4. ለሌሎች በምናነብበት ወቅት በምናነበው ጽሑፍ ውስጥ ላሉት ዋና ዋና ነጥቦች ለየት ያለ አጽንዖት መስጠት የምንችለው እንዴት ነው? [be ገጽ 105 አን. 1-6]
5. በምናስተምርበት ጊዜ ተስማሚ የድምፅ መጠን መጠቀማችን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? የድምፃችን መጠን ምን ያህል መሆን እንዳለበት ለመወሰን ምን ሊረዳን ይችላል? [be ገጽ 107-108]
ክፍል ቁጥር 1
6. በዘመናችን የሚገኙት ክርስቲያኖች ያሉበት ሁኔታ መርዶክዮስና አስቴር ይኖሩበት ከነበረው ጊዜ ጋር ተመሳሳይ የሆነው በምን መልኩ ነው? ምሳሌነታቸውንስ እንዴት ልንኮርጅ እንችላለን? [bsi ገጽ 11 አን. 17]
7. ሰሎሞን “ሁሉም ከንቱ፣ ነፋስንም እንደ መከተል ነበር” ሲል ስለ ምን መናገሩ ነበር? (መክ. 2:11) [w04 10/15 ገጽ 4 አን. 3-4]
8. ለይሖዋ ፍቅር ማዳበር የምንችለው እንዴት ነው? (ማር. 12:30) [w04 3/1 ገጽ 19-21]
9. በመንፈሳዊ እሴቶችና ቁሳዊ ሀብትን በማሳደድ መካከል ምን ልዩነት አለ? [w04 10/15 ገጽ 5-7]
10. በጉባኤም ሆነ በትልልቅ ስብሰባዎች ላይ ትኩረታችን ሳይከፋፈል በጥሞና ለማዳመጥ ምን ሊረዳን ይችላል? [be ገጽ 15-16]
ሳምንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ
11. የሐማ ፊት የተሸፈነው ለምን ነበር? (አስቴር 7:8)
12. በኤልፋዝ አስተሳሰብ ላይ ተጽዕኖ አድርጎ የነበረው ምን ዓይነት መንፈስ ነው? (ኢዮብ 4:15, 16) [w05 9/15 ገጽ 26 አን. 2]
13. በኢዮብ 7:9, 10 እንዲሁም ኢዮብ 10:21 ላይ የተመዘገቡት አገላለጾች ኢዮብ በትንሣኤ እንደማያምን ያመለክታሉ?
14. “የጥርሴ ቆዳ ብቻ ቀርቶ አመለጥሁ” የሚለው የኢዮብ አባባል ምን ያመለክታል? (ኢዮብ 19:20 NW)
15. ኢዮብ “ጨዋነቴንም [“ታማኝነቴን፣” NW] እስክሞት ድረስ አልጥልም” ሲል ምን ማለቱ ነበር? እኛስ ከዚህ ምን እንማራለን? (ኢዮብ 27:5)
-
-
በጥናቶችህ አማካኝነት ጥናት ለማግኘት ሞክረሃል?የመንግሥት አገልግሎት—2006 | ሚያዝያ
-
-
በጥናቶችህ አማካኝነት ጥናት ለማግኘት ሞክረሃል?
በአሁኑ ወቅት ጥናት ካለህ መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚያስተምር ለማወቅ የሚፈልጉ ጓደኞች ወይም ዘመዶች ይኖሩት እንደሆነ አሊያም የሚያውቃቸው ሰዎች እንዳሉ ለምን አትጠይቀውም? አብዛኛውን ጊዜ የተወሰኑ ሰዎችን ሊጠቁምህ ይችላል። እነዚህ ሰዎች ጋር ሄደህ መጽሐፍ ቅዱስን እንዲያጠኑ ግብዣ በምታቀርብበት ጊዜ ጥናትህ ፈቃደኛ ከሆነ እሱ እንደላከህ መጥቀስ ትችላለህ። እንዲህ ልትል ትችላለህ:- “[የጥናትህ ስም] መጽሐፍ ቅዱስ ማጥናቱን የወደደው ሲሆን እርስዎም ያለ ክፍያ ከምናደርገው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮግራም ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ያስባል።” ከዚያም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የተባለውን መጽሐፍ በመጠቀም ጥናቱ እንዴት እንደሚካሄድ አጠር አድርገህ አሳያቸው።
ጥሩ እድገት በማድረግ ላይ ያለ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ ካለህ ስለ አምላክ ቃል ማወቅ ለሚፈልጉ ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ጥናቱ እንዴት እንደሚካሄድ እንዲናገር ልታበረታታው ትችላለህ። በጥናቱም ወቅት እንዲገኙ ሊጋብዛቸው ይችላል። ይህ አመቺ ካልሆነ ደግሞ ከእነሱ ጋር ተገናኝተህ ጥናቱ እንዴት እንደሚካሄድ እንድታሳያቸው ቀጠሮ ሊይዝልህ ይችላል። እንዲህ ማድረጉ ተማሪው የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀቱን ለሌሎች ማካፈል እንዲጀምር ሊያበረታታው ይችላል።
በተጨማሪም በቋሚነት ተመላልሶ መጠየቅ የምታደርግላቸው ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ባይጀምሩም እንኳ በእነሱ አማካኝነት ጥናት ልታገኝ ትችላለህ። የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የተባለውን መጽሐፍ ስታበረክትላቸው “ይህን ጽሑፍ ማግኘት የሚፈልግ ሌላ የሚያውቁት ሰው ይኖር ይሆን?” ብለህ መጠየቅ ትችላለህ።
የጊዜውን አጣዳፊነት ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ሰዎች ምሥራቹን እንዲሰሙና እንዲቀበሉ መርዳት የምንችልበትን ማንኛውንም መንገድ መጠቀም እንፈልጋለን። ታዲያ አንተስ በጥናቶችህ አማካኝነት ጥናት ለማግኘት ሞክረሃል?
-