የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መዝሙር 109
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

መዝሙር የመጽሐፉ ይዘት

      • የተጨነቀ ሰው ያቀረበው ጸሎት

        • “ሹመቱን ሌላ ሰው ይውሰደው” (8)

        • አምላክ በድሃው ቀኝ ይቆማል (31)

መዝሙር 109:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 33:1

መዝሙር 109:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 15:2, 3፤ መዝ 31:18

መዝሙር 109:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 15:12፤ 16:5-7፤ መዝ 69:4

መዝሙር 109:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 13:39

መዝሙር 109:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 35:11, 12፤ 38:19, 20፤ 55:12-14

መዝሙር 109:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከሳሽ።”

መዝሙር 109:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ክፉ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 1:15፤ ሚክ 3:4

መዝሙር 109:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 55:23፤ ማቴ 27:5
  • +ሥራ 1:16-20

መዝሙር 109:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ወንዶች ልጆቹ።”

መዝሙር 109:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ወንዶች ልጆቹ።”

መዝሙር 109:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “አራጣ አበዳሪዎች ወጥመድ ይዘርጉበት።”

መዝሙር 109:12

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ታማኝ ፍቅር።”

መዝሙር 109:13

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ትውልዱ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 37:28

መዝሙር 109:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 3:28, 29፤ 21:1

መዝሙር 109:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 34:16

መዝሙር 109:16

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ታማኝ ፍቅር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ያዕ 2:13
  • +2ሳሙ 16:11፤ 17:1, 2፤ መዝ 10:2፤ 37:32

መዝሙር 109:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 109:29

መዝሙር 109:20

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በነፍሴም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 17:23

መዝሙር 109:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 25:11፤ 31:3
  • +መዝ 36:7፤ 69:16፤ 86:5

መዝሙር 109:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 40:17
  • +መዝ 102:4

መዝሙር 109:24

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ሥጋዬ ኮሰመነ፤ ስብም (ዘይትም) የለውም።”

መዝሙር 109:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 31:11
  • +መዝ 22:7፤ ማቴ 27:39

መዝሙር 109:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እጅጌ እንደሌለው ቀሚስ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 35:26

መዝሙር 109:30

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 22:22

መዝሙር 109:31

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በነፍሱ።”

ተዛማጅ ሐሳብ

መዝ. 109:1መዝ 33:1
መዝ. 109:22ሳሙ 15:2, 3፤ መዝ 31:18
መዝ. 109:32ሳሙ 15:12፤ 16:5-7፤ መዝ 69:4
መዝ. 109:42ሳሙ 13:39
መዝ. 109:5መዝ 35:11, 12፤ 38:19, 20፤ 55:12-14
መዝ. 109:7ኢሳ 1:15፤ ሚክ 3:4
መዝ. 109:8መዝ 55:23፤ ማቴ 27:5
መዝ. 109:8ሥራ 1:16-20
መዝ. 109:13መዝ 37:28
መዝ. 109:142ሳሙ 3:28, 29፤ 21:1
መዝ. 109:15መዝ 34:16
መዝ. 109:16ያዕ 2:13
መዝ. 109:162ሳሙ 16:11፤ 17:1, 2፤ መዝ 10:2፤ 37:32
መዝ. 109:19መዝ 109:29
መዝ. 109:202ሳሙ 17:23
መዝ. 109:21መዝ 25:11፤ 31:3
መዝ. 109:21መዝ 36:7፤ 69:16፤ 86:5
መዝ. 109:22መዝ 40:17
መዝ. 109:22መዝ 102:4
መዝ. 109:25መዝ 31:11
መዝ. 109:25መዝ 22:7፤ ማቴ 27:39
መዝ. 109:29መዝ 35:26
መዝ. 109:30መዝ 22:22
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
መዝሙር 109:1-31

መዝሙር

ለሙዚቀኞች ቡድን መሪ። የዳዊት መዝሙር። ማህሌት።

109 የማወድስህ አምላክ ሆይ፣+ ዝም አትበል።

 2 ክፉዎችና አታላዮች በእኔ ላይ አፋቸውን ይከፍታሉና።

ስለ እኔ በሐሰተኛ አንደበት ይናገራሉ፤+

 3 በዙሪያዬም ሆነው የጥላቻ ቃላት ይሰነዝሩብኛል፤

ያለምክንያት ያጠቁኛል።+

 4 ፍቅር ሳሳያቸው በምላሹ ይቃወሙኛል፤+

እኔ ግን መጸለዬን እቀጥላለሁ።

 5 ለመልካም ነገር ክፋትን፣

ላሳየኋቸው ፍቅር ጥላቻን ይመልሱልኛል።+

 6 በእሱ ላይ ክፉ ሰው እዘዝበት፤

በቀኙም ተቃዋሚ* ይቁም።

 7 ፍርድ ፊት ሲቆም በደለኛ* ሆኖ ይገኝ፤

ጸሎቱም እንኳ እንደ ኃጢአት ይቆጠርበት።+

 8 የሕይወት ዘመኑ አጭር ይሁን፤+

የበላይ ተመልካችነት ሹመቱን ሌላ ሰው ይውሰደው።+

 9 ልጆቹ* ያለአባት ይቅሩ፤

ሚስቱም መበለት ትሁን።

10 ልጆቹ* በየቦታው የሚቅበዘበዙ ለማኞች ይሁኑ፤

ከፈራረሰው መኖሪያቸው ወጥተው ምግብ ፍለጋ ይንከራተቱ።

11 ያበደረው ሰው ያለውን ነገር ሁሉ ይውሰድበት፤*

ባዕድ ሰዎችም ንብረቱን ይዝረፉት።

12 ደግነት* የሚያሳየው ሰው ከቶ አይኑር፤

ያለአባት ለቀሩት ልጆቹ የሚራራ አንድም ሰው አይገኝ።

13 ዘሩ* ይጥፋ፤+

ስማቸው በአንድ ትውልድ ውስጥ ይደምሰስ።

14 አባቶቹ የሠሩትን በደል ይሖዋ አይርሳ፤+

የእናቱም ኃጢአት አይደምሰስ።

15 ይሖዋ የሠሩትን ነገር ምንጊዜም ያስብ፤

መታሰቢያቸውንም ከምድር ገጽ ያጥፋ።+

16 ክፉው ሰው ደግነት* ለማሳየት አላሰበምና፤+

ይልቁንም የተጨቆነውን፣ ድሃውንና ልቡ በሐዘን የተደቆሰውን ሰው

ለመግደል ሲያሳድድ ነበር።+

17 ሌሎችን መርገም ወደደ፤ በመሆኑም እርግማኑ በእሱ ላይ ደረሰበት፤

ሌሎችን ለመባረክ ፍላጎት አልነበረውም፤ ስለዚህ ምንም በረከት አላገኘም።

18 እርግማንን እንደ ልብስ ለበሰ።

እንደ ውኃም ሰውነቱ ውስጥ ፈሰሰ፤

እንደ ዘይት ወደ አጥንቶቹ ዘለቀ።

19 እርግማኑ እንደሚከናነበው ልብስ፣

ሁልጊዜ እንደሚታጠቀውም ቀበቶ ይሁንለት።+

20 እኔን የሚቃወመኝ ሰው፣

በእኔም* ላይ ክፉ ነገር የሚናገሩ ሰዎች ከይሖዋ የሚያገኙት ዋጋ ይህ ነው።+

21 አንተ ግን ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣

ለስምህ ስትል እርዳኝ።+

ታማኝ ፍቅርህ ጥሩ ስለሆነ ታደገኝ።+

22 እኔ ምስኪንና ድሃ ነኝና፤+

ልቤም በውስጤ ተወግቷል።+

23 ፀሐይ ስትጠልቅ እንደሚጠፋ ጥላ አልፋለሁ፤

እንደ አንበጣ አራግፈው ጣሉኝ።

24 ከመጾሜ የተነሳ ጉልበቶቼ ከዱኝ፤

ሰውነቴ ከሳ፤ እኔም እየመነመንኩ ሄድኩ።*

25 የእነሱ መሳለቂያ ሆንኩ።+

ሲያዩኝ ራሳቸውን ይነቀንቃሉ።+

26 ይሖዋ አምላኬ ሆይ፣ እርዳኝ፤

በታማኝ ፍቅርህ አድነኝ።

27 ይህ የአንተ እጅ መሆኑን ይወቁ፤

ይሖዋ ሆይ፣ ይህን ያደረግከው አንተ እንደሆንክ ይገንዘቡ።

28 እነሱ ይራገሙ፤ አንተ ግን ባርክ።

እነሱ በእኔ ላይ ሲነሱ ለኀፍረት ይዳረጉ፤

አገልጋይህ ግን ሐሴት ያድርግ።

29 እኔን የሚቃወሙኝ ውርደት ይከናነቡ፤

ኀፍረታቸውንም እንደ ልብስ* ይጎናጸፉ።+

30 አንደበቴ ይሖዋን ከልብ ታወድሰዋለች፤

በብዙ ሕዝቦች ፊት አወድሰዋለሁ።+

31 በእሱ* ላይ ከሚፈርዱት ሊያድነው

በድሃው ቀኝ ይቆማልና።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ