የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መኃልየ መኃልይ 3
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

መኃልየ መኃልይ የመጽሐፉ ይዘት

    • ሱላማዊቷ ልጃገረድ በንጉሥ ሰለሞን ሰፈር (1:1–3:5)

    • ሱላማዊቷ በኢየሩሳሌም (3:6–8:4)

        • የጽዮን ሴቶች ልጆች (6-11)

          • የሰለሞን አጀብ

መኃልየ መኃልይ 3:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ የምትወደውን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መኃ 1:7
  • +መኃ 5:6

መኃልየ መኃልይ 3:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ የምትወደውን።”

መኃልየ መኃልይ 3:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ የምትወደውን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መኃ 5:7

መኃልየ መኃልይ 3:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ የምትወደውን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መኃ 8:2

መኃልየ መኃልይ 3:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መኃ 2:7፤ 8:4

መኃልየ መኃልይ 3:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 30:23, 24, 34

መኃልየ መኃልይ 3:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 9:22

መኃልየ መኃልይ 3:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ከፍተኛ ሥልጣን ያለውን ሰው ተሸክሞ ለመውሰድ የሚያገለግል መሸፈኛ ያለው ድንክ አልጋ።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 5:8, 9

መኃልየ መኃልይ 3:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የአበባ ጉንጉን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 12:24፤ ምሳሌ 4:3

ተዛማጅ ሐሳብ

መኃ. 3:1መኃ 1:7
መኃ. 3:1መኃ 5:6
መኃ. 3:3መኃ 5:7
መኃ. 3:4መኃ 8:2
መኃ. 3:5መኃ 2:7፤ 8:4
መኃ. 3:6ዘፀ 30:23, 24, 34
መኃ. 3:71ነገ 9:22
መኃ. 3:91ነገ 5:8, 9
መኃ. 3:112ሳሙ 12:24፤ ምሳሌ 4:3
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
መኃልየ መኃልይ 3:1-11

መኃልየ መኃልይ

3 “ሌሊት በአልጋዬ ላይ ሆኜ

የምወደውን* ሰው ለማግኘት ተመኘሁ።+

ፈለግኩት፤ ግን አላገኘሁትም።+

 2 ተነስቼ በከተማዋ ውስጥ እዘዋወራለሁ፤

የምወደውን* ሰው

እስቲ በጎዳናዎቹና በአደባባዮቹ ልፈልገው።

ፈለግኩት፤ ግን አላገኘሁትም።

 3 በከተማዋ ውስጥ የሚዘዋወሩት ጠባቂዎች አገኙኝ።+

እኔም ‘የምወደውን* ሰው አይታችሁታል?’ ብዬ ጠየቅኳቸው።

 4 ከእነሱ ገና እልፍ እንዳልኩ

የምወደውን* ሰው አገኘሁት።

አጥብቄም ያዝኩት፤

ወደ እናቴ ቤት፣ ወደ ፀነሰችኝም ሴት እልፍኝ

እስካስገባው ድረስ አለቀኩትም።+

 5 የኢየሩሳሌም ሴቶች ልጆች ሆይ፣ በራሱ እስኪነሳሳ ድረስ

ፍቅርን በውስጤ እንዳትቀሰቅሱ ወይም እንዳታነሳሱ

በሜዳ ፍየሎችና በመስክ ላይ ባሉ አጋዘኖች አምላችኋለሁ።”+

 6 “በከርቤና በነጭ ዕጣን፣

ጥሩ መዓዛ ባላቸውም የነጋዴ ቅመማ ቅመሞች ታውዶ፣+

እንደ ጭስ ዓምድ ከምድረ በዳ እየመጣ ያለው ይህ ነገር ምንድን ነው?”

 7 “እነሆ፣ ይህ የሰለሞን ድንክ አልጋ ነው።

ከእስራኤል ኃያላን የተውጣጡ

ስልሳ ኃያላን አጅበውታል፤+

 8 ሁሉም ሰይፍ የታጠቁና

በውጊያ የሠለጠኑ ናቸው፤

እያንዳንዳቸውም በሌሊት የሚያጋጥሙ አስፈሪ ነገሮችን ለመከላከል

ሰይፋቸውን ወገባቸው ላይ ታጥቀዋል።”

 9 “ይህ፣ ንጉሥ ሰለሞን ከሊባኖስ እንጨት+

ለራሱ ያሠራው የንጉሥ ድንክ አልጋ* ነው።

10 ዓምዶቹን የሠራው ከብር፣

መደገፊያዎቹን ደግሞ ከወርቅ ነው።

መቀመጫው በሐምራዊ ሱፍ የተሠራ ነው፤

ውስጡንም የኢየሩሳሌም ሴቶች ልጆች

በፍቅር ተነሳስተው ለብጠውታል።”

11 “እናንተ የጽዮን ሴቶች ልጆች ሆይ፣

ወጥታችሁ ንጉሥ ሰለሞንን ተመልከቱ፤

በሠርጉ ዕለት፣

ልቡ ሐሴት ባደረገበት በዚያ ቀን፣

እናቱ+ የሠራችለትን የሠርግ አክሊል* ደፍቷል።”

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ