መኃልየ መኃልይ
ፈለግኩት፤ ግን አላገኘሁትም።+
ፈለግኩት፤ ግን አላገኘሁትም።
3 በከተማዋ ውስጥ የሚዘዋወሩት ጠባቂዎች አገኙኝ።+
እኔም ‘የምወደውን* ሰው አይታችሁታል?’ ብዬ ጠየቅኳቸው።
4 ከእነሱ ገና እልፍ እንዳልኩ
የምወደውን* ሰው አገኘሁት።
5 የኢየሩሳሌም ሴቶች ልጆች ሆይ፣ በራሱ እስኪነሳሳ ድረስ
ፍቅርን በውስጤ እንዳትቀሰቅሱ ወይም እንዳታነሳሱ
በሜዳ ፍየሎችና በመስክ ላይ ባሉ አጋዘኖች አምላችኋለሁ።”+
7 “እነሆ፣ ይህ የሰለሞን ድንክ አልጋ ነው።
ከእስራኤል ኃያላን የተውጣጡ
ስልሳ ኃያላን አጅበውታል፤+
8 ሁሉም ሰይፍ የታጠቁና
በውጊያ የሠለጠኑ ናቸው፤
እያንዳንዳቸውም በሌሊት የሚያጋጥሙ አስፈሪ ነገሮችን ለመከላከል
ሰይፋቸውን ወገባቸው ላይ ታጥቀዋል።”
10 ዓምዶቹን የሠራው ከብር፣
መደገፊያዎቹን ደግሞ ከወርቅ ነው።
መቀመጫው በሐምራዊ ሱፍ የተሠራ ነው፤
ውስጡንም የኢየሩሳሌም ሴቶች ልጆች
በፍቅር ተነሳስተው ለብጠውታል።”