የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 1 ሳሙኤል 18
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

1 ሳሙኤል የመጽሐፉ ይዘት

      • የዳዊትና የዮናታን ወዳጅነት (1-4)

      • ሳኦል፣ ዳዊት ባገኘው ድል ቀና (5-9)

      • ሳኦል ዳዊትን ሊገድለው ሞከረ (10-19)

      • ዳዊት የሳኦልን ልጅ ሜልኮልን አገባ (20-30)

1 ሳሙኤል 18:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የዮናታን ነፍስ ከዳዊት ነፍስ ጋር ተቆራኘች።”

  • *

    ወይም “እንደ ገዛ ነፍሱ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 14:1, 49
  • +1ሳሙ 19:2፤ 20:17, 41፤ 2ሳሙ 1:26

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    በእምነታቸው ምሰሏቸው፣ ርዕስ 3

    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)፣

    1/2021፣ ገጽ 21-22

    ለዘላለም በደስታ ኑር!፣ ትምህርት 48

1 ሳሙኤል 18:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 8:11፤ 16:22፤ 17:15

1 ሳሙኤል 18:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እንደ ገዛ ነፍሱ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ምሳሌ 17:17፤ 18:24
  • +1ሳሙ 20:8, 42፤ 23:18፤ 2ሳሙ 9:1፤ 21:7

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    በእምነታቸው ምሰሏቸው፣ ርዕስ 3

1 ሳሙኤል 18:4

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    በእምነታቸው ምሰሏቸው፣ ርዕስ 3

1 ሳሙኤል 18:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ተልእኮውን በጥበብ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:30
  • +1ሳሙ 14:52

1 ሳሙኤል 18:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መሳ 11:34
  • +ዘፀ 15:20, 21፤ መሳ 5:1

1 ሳሙኤል 18:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 21:11፤ 29:5

1 ሳሙኤል 18:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 4:5፤ ምሳሌ 14:30
  • +1ሳሙ 13:14፤ 15:27, 28፤ 16:13፤ 20:31፤ 24:17, 20

1 ሳሙኤል 18:9

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    በእምነታቸው ምሰሏቸው፣ ርዕስ 3

1 ሳሙኤል 18:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እንደ ነቢይ ያደርገው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 16:14
  • +1ሳሙ 16:16, 23
  • +1ሳሙ 19:9, 10

1 ሳሙኤል 18:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 20:33

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    9/15/2008፣ ገጽ 4

1 ሳሙኤል 18:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 16:14
  • +1ሳሙ 18:28, 29

1 ሳሙኤል 18:13

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “በሕዝቡ ፊት ይወጣና ይገባ ነበር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 5:2

1 ሳሙኤል 18:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የሚያከናውነውን ነገር ሁሉ በጥበብ ያደርግ ነበር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:5
  • +ዘፍ 39:2፤ ኢያሱ 6:27፤ 1ሳሙ 10:7፤ 16:18

1 ሳሙኤል 18:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 14:49
  • +1ሳሙ 17:25
  • +1ሳሙ 25:28
  • +1ሳሙ 18:25

1 ሳሙኤል 18:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 7:18

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    4/1/2004፣ ገጽ 15

1 ሳሙኤል 18:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 21:8

1 ሳሙኤል 18:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 14:49፤ 19:11፤ 25:44፤ 2ሳሙ 3:13፤ 6:16

1 ሳሙኤል 18:21

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “አማቼ ትሆናለህ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:17

1 ሳሙኤል 18:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:18

1 ሳሙኤል 18:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 29:18
  • +1ሳሙ 17:26, 36፤ 2ሳሙ 3:14

1 ሳሙኤል 18:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:21

1 ሳሙኤል 18:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 17:25

1 ሳሙኤል 18:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 16:13፤ 24:17, 20
  • +1ሳሙ 18:20

1 ሳሙኤል 18:29

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:9, 12፤ 20:33

1 ሳሙኤል 18:30

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በጥበብ ይመላለስ ነበር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:5
  • +2ሳሙ 7:9

ተዛማጅ ሐሳብ

1 ሳሙ. 18:11ሳሙ 14:1, 49
1 ሳሙ. 18:11ሳሙ 19:2፤ 20:17, 41፤ 2ሳሙ 1:26
1 ሳሙ. 18:21ሳሙ 8:11፤ 16:22፤ 17:15
1 ሳሙ. 18:3ምሳሌ 17:17፤ 18:24
1 ሳሙ. 18:31ሳሙ 20:8, 42፤ 23:18፤ 2ሳሙ 9:1፤ 21:7
1 ሳሙ. 18:51ሳሙ 18:30
1 ሳሙ. 18:51ሳሙ 14:52
1 ሳሙ. 18:6መሳ 11:34
1 ሳሙ. 18:6ዘፀ 15:20, 21፤ መሳ 5:1
1 ሳሙ. 18:71ሳሙ 21:11፤ 29:5
1 ሳሙ. 18:8ዘፍ 4:5፤ ምሳሌ 14:30
1 ሳሙ. 18:81ሳሙ 13:14፤ 15:27, 28፤ 16:13፤ 20:31፤ 24:17, 20
1 ሳሙ. 18:101ሳሙ 16:14
1 ሳሙ. 18:101ሳሙ 16:16, 23
1 ሳሙ. 18:101ሳሙ 19:9, 10
1 ሳሙ. 18:111ሳሙ 20:33
1 ሳሙ. 18:121ሳሙ 16:14
1 ሳሙ. 18:121ሳሙ 18:28, 29
1 ሳሙ. 18:132ሳሙ 5:2
1 ሳሙ. 18:141ሳሙ 18:5
1 ሳሙ. 18:14ዘፍ 39:2፤ ኢያሱ 6:27፤ 1ሳሙ 10:7፤ 16:18
1 ሳሙ. 18:171ሳሙ 14:49
1 ሳሙ. 18:171ሳሙ 17:25
1 ሳሙ. 18:171ሳሙ 25:28
1 ሳሙ. 18:171ሳሙ 18:25
1 ሳሙ. 18:182ሳሙ 7:18
1 ሳሙ. 18:192ሳሙ 21:8
1 ሳሙ. 18:201ሳሙ 14:49፤ 19:11፤ 25:44፤ 2ሳሙ 3:13፤ 6:16
1 ሳሙ. 18:211ሳሙ 18:17
1 ሳሙ. 18:231ሳሙ 18:18
1 ሳሙ. 18:25ዘፍ 29:18
1 ሳሙ. 18:251ሳሙ 17:26, 36፤ 2ሳሙ 3:14
1 ሳሙ. 18:261ሳሙ 18:21
1 ሳሙ. 18:271ሳሙ 17:25
1 ሳሙ. 18:281ሳሙ 16:13፤ 24:17, 20
1 ሳሙ. 18:281ሳሙ 18:20
1 ሳሙ. 18:291ሳሙ 18:9, 12፤ 20:33
1 ሳሙ. 18:301ሳሙ 18:5
1 ሳሙ. 18:302ሳሙ 7:9
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
1 ሳሙኤል 18:1-30

አንደኛ ሳሙኤል

18 ዳዊት ከሳኦል ጋር ተነጋግሮ እንደጨረሰ ዮናታንና+ ዳዊት የጠበቀ ወዳጅነት መሠረቱ፤* ዮናታንም እንደ ራሱ* ወደደው።+ 2 ከዚያን ቀን ጀምሮ ሳኦል ዳዊት ከእሱ ጋር እንዲኖር አደረገ፤ ወደ አባቱም ቤት እንዲመለስ አልፈቀደለትም።+ 3 ዮናታንም ዳዊትን እንደ ራሱ* ስለወደደው+ ከዳዊት ጋር ቃል ኪዳን ተጋቡ።+ 4 ከዚያም ዮናታን ለብሶት የነበረውን መደረቢያ አውልቆ ለዳዊት ሰጠው፤ እንዲሁም ልብሶቹን ሌላው ቀርቶ ሰይፉን፣ ቀስቱንና ቀበቶውን ሰጠው። 5 ዳዊትም ለውጊያ ይወጣ ጀመር፤ ሳኦል በሚልከው በማንኛውም ቦታ ተልእኮውን በተሳካ ሁኔታ* ይፈጽም ነበር።+ በመሆኑም ሳኦል በሠራዊቱ ላይ ሾመው፤+ ይህም ሕዝቡንና የሳኦልን አገልጋዮች በሙሉ አስደሰታቸው።

6 ዳዊትና አብረውት ያሉት ሰዎች ፍልስጤማውያንን መትተው በተመለሱ ጊዜ በመላው የእስራኤል ከተሞች የሚገኙ ሴቶች አታሞና+ ባለ ሦስት አውታር መሣሪያ ይዘው በደስታ እየዘፈኑና+ እየጨፈሩ ንጉሥ ሳኦልን ለመቀበል ወጡ። 7 እየጨፈሩ የነበሩት ሴቶችም እንዲህ እያሉ ዘፈኑ፦

“ሳኦል ሺዎችን ገደለ፤

ዳዊት ደግሞ አሥር ሺዎችን ገደለ።”+

8 ሳኦልም እጅግ ተቆጣ፤+ ዘፈኑም አላስደሰተውም፤ በመሆኑም “ለዳዊት አሥር ሺህ አሉለት፤ ለእኔ ግን ሺህ ብቻ፤ ያልተሰጠው ነገር እኮ መንግሥት ብቻ ነው!” አለ።+ 9 ከዚያች ዕለት አንስቶ ሳኦል ዳዊትን በጥርጣሬ ዓይን ይመለከተው ጀመር።

10 በማግስቱም ከአምላክ የመጣ መጥፎ መንፈስ ሳኦልን ያዘው፤+ ዳዊት በፊት እንደሚያደርገው ሁሉ በገና እየደረደረ+ ሳለ ሳኦል ቤቱ ውስጥ እንግዳ ባሕርይ ያሳይ* ጀመር። ሳኦልም በእጁ ጦር ይዞ ነበር፤+ 11 እሱም ‘ዳዊትን ከግድግዳው ጋር አጣብቀዋለሁ!’ ብሎ በማሰብ ጦሩን በኃይል ወረወረው።+ ዳዊት ግን ሁለት ጊዜ ከእሱ አመለጠ። 12 ይሖዋ ከሳኦል ተለይቶ+ ከዳዊት ጋር ስለነበር+ ሳኦል ዳዊትን ፈራው። 13 በመሆኑም ሳኦል ከፊቱ እንዲርቅ አደረገው፤ የሺህ አለቃ አድርጎም ሾመው፤ ዳዊትም ሠራዊቱን እየመራ ወደ ጦርነት ይሄድ ነበር።*+ 14 ዳዊት የሚያከናውነው ነገር ሁሉ ይሳካለት ነበር፤*+ ይሖዋም ከእሱ ጋር ነበር።+ 15 ሳኦልም ዳዊት ስኬታማ እንደሆነ ሲያይ ፈራው። 16 መላው እስራኤልና ይሁዳ ግን ዳዊትን ወደዱት፤ ምክንያቱም ወደ ጦርነት ሲወጡ የሚመራቸው እሱ ነበር።

17 በኋላም ሳኦል ዳዊትን እንዲህ አለው፦ “እንግዲህ ትልቋ ልጄ ሜሮብ+ አለች። እሷን እድርልሃለሁ።+ ሆኖም ጀግንነትህን ለእኔ ከማሳየት ወደኋላ ማለት የለብህም፤ የይሖዋንም ጦርነቶች መዋጋት ይኖርብሃል።”+ ሳኦል ይህን ያለው ‘እጄን በዚህ ሰው ላይ አላሳርፍም። ከዚህ ይልቅ በፍልስጤማውያን እጅ ይሙት’ ብሎ ስላሰበ ነው።+ 18 በዚህ ጊዜ ዳዊት ሳኦልን “ለንጉሡ አማች እሆን ዘንድ እኔም ሆንኩ የአባቴ ቤተሰቦች የሆኑት ዘመዶቼ በእስራኤል ውስጥ ከቶ ማን ሆነን ነው?” አለው።+ 19 ሆኖም የሳኦል ልጅ ሜሮብ ለዳዊት ልትሰጥ የነበረበት ጊዜ ሲደርስ እሷ ቀድሞውኑ ለመሆላታዊው ለአድሪዔል+ ተድራ ነበር።

20 የሳኦል ልጅ ሜልኮል+ ዳዊትን ትወደው ነበር፤ ይህን ለሳኦል ነገሩት፤ እሱም ነገሩ ደስ አሰኘው። 21 በመሆኑም ሳኦል “ወጥመድ እንድትሆነውና የፍልስጤማውያን እጅ በእሱ ላይ እንዲሆን እሷን እሰጠዋለሁ” አለ።+ ከዚያም ሳኦል ለሁለተኛ ጊዜ ዳዊትን “በዛሬዋ ዕለት በዚህች በሁለተኛዋ ሴት አማካኝነት ከእኔ ጋር በጋብቻ ትዛመዳለህ”* አለው። 22 በተጨማሪም ሳኦል አገልጋዮቹን እንዲህ ሲል አዘዛቸው፦ “ለዳዊት እንዲህ ብላችሁ በሚስጥር ንገሩት፦ ‘ንጉሡ በአንተ ደስ ብሎታል፤ አገልጋዮቹም በሙሉ ይወዱሃል። ስለሆነም አሁን ከንጉሡ ጋር በጋብቻ ተዛመድ።’” 23 የሳኦልም አገልጋዮች ይህን በነገሩት ጊዜ ዳዊት “እዚህ ግባ ለማልባል ለእንደኔ ዓይነቱ ድሃ ከንጉሡ ጋር በጋብቻ መዛመድ እንዲህ ቀላል ነገር ይመስላችኋል?” አላቸው።+ 24 ከዚያም የሳኦል አገልጋዮች “ዳዊት እኮ እንዲህ እንዲህ አለ” ብለው ነገሩት።

25 በዚህ ጊዜ ሳኦል እንዲህ አለ፦ “ዳዊትን እንዲህ በሉት፦ ‘ንጉሡ ከአንተ የሚፈልገው ጥሎሽ+ ሳይሆን ጠላቶቹን መበቀል እንዲችል የ100 ፍልስጤማውያንን ሸለፈት+ ብቻ ነው።’” ሳኦል ይህን ያለው ዳዊት በፍልስጤማውያን እጅ እንዲወድቅ ተንኮል አስቦ ስለነበር ነው። 26 በመሆኑም አገልጋዮቹ ይህንኑ ለዳዊት ነገሩት፤ ዳዊትም ከንጉሡ ጋር በጋብቻ የመዛመዱ ጉዳይ አስደሰተው።+ ስለሆነም የተሰጠው ጊዜ ከማብቃቱ በፊት 27 ዳዊት አብረውት ከነበሩት ሰዎች ጋር በመሄድ 200 ፍልስጤማውያንን መታ፤ ዳዊት ከንጉሡ ጋር በጋብቻ ለመዛመድ የገደላቸውን ሰዎች ሸለፈት በሙሉ አምጥቶ ለንጉሡ ሰጠው። በመሆኑም ሳኦል ልጁን ሜልኮልን ዳረለት።+ 28 ሳኦል ይሖዋ ከዳዊት ጋር እንደነበርና+ ልጁ ሜልኮልም ዳዊትን እንደወደደችው+ ተረዳ። 29 በዚህም ምክንያት ሳኦል ዳዊትን ከበፊቱ ይልቅ ፈራው፤ በመሆኑም ዕድሜውን ሙሉ የዳዊት ጠላት ሆነ።+

30 የፍልስጤም መኳንንትም ለውጊያ ይወጡ ነበር፤ ሆኖም ለውጊያ በወጡ ቁጥር ዳዊት ከሳኦል አገልጋዮች ሁሉ ይበልጥ ይሳካለት ነበር፤*+ ስሙም እየገነነ መጣ።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ