ዘዳግም 28:49, 50 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 49 “ይሖዋ ቋንቋውን የማትረዳውን+ በሩቅ ያለን አንድ ብሔር ከምድር ጫፍ አስነስቶ ያመጣብሃል፤+ እሱም እንደ ንስር ተምዘግዝጎ ይወርድብሃል፤+ 50 ይህ ብሔር ለሽማግሌ የማያዝን ወይም ለወጣት የማይራራ ፊቱ የሚያስፈራ ብሔር ነው።+ 2 ነገሥት 15:29 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 29 በእስራኤል ንጉሥ በፋቁሄ ዘመን የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር+ ወረራ በማካሄድ ኢዮንን፣ አቤልቤትማዓካን፣+ ያኖአህን፣ ቃዴሽን፣+ ሃጾርን፣ ጊልያድን+ እንዲሁም ገሊላን ይኸውም መላውን የንፍታሌም+ ምድር ያዘ፤ ነዋሪዎቹንም በግዞት ወደ አሦር ወሰደ።+ 2 ነገሥት 17:6 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 6 ሆሺአ በነገሠ በዘጠነኛው ዓመት የአሦር ንጉሥ ሰማርያን ያዘ።+ ከዚያም የእስራኤልን ሕዝብ ወደ አሦር በግዞት+ በመውሰድ በሃላህ፣ በጎዛን+ ወንዝ አጠገብ በምትገኘው በሃቦርና በሜዶናውያን ከተሞች አሰፈራቸው።+ ኢሳይያስ 7:20 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 20 “በዚያም ቀን ይሖዋ በወንዙ* አካባቢ ከሚገኘው ቦታ በተከራየው ምላጭ ይኸውም በአሦር ንጉሥ+ አማካኝነት ራሱንና የእግሩን ፀጉር ይላጨዋል፤ ጢሙንም ሙልጭ አድርጎ ያስወግደዋል። ኢሳይያስ 8:4 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 4 ልጁ ‘አባዬ!’ እና ‘እማዬ!’ ብሎ መጥራት ከመቻሉ በፊት የደማስቆ ሀብትና የሰማርያ ምርኮ በአሦር ንጉሥ ፊት ይወሰዳል።”+ ኢሳይያስ 10:5, 6 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 5 “የቁጣዬ በትር የሆነውንና+ውግዘቴን የምገልጽበትን ዱላ በእጁ የያዘውንአሦራዊ+ ተመልከት! 6 ከሃዲ በሆነው ብሔር ላይ፣እጅግ ባስቆጣኝም ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፤+ብዙ ምርኮ እንዲወስድ፣ ብዙ ሀብት እንዲዘርፍናሕዝቡን በጎዳናዎች ላይ እንዳለ ጭቃ እንዲረጋግጥ አዘዋለሁ።+ ሆሴዕ 10:6 አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ 6 ለአንድ ታላቅ ንጉሥ እንደሚቀርብ ስጦታ ወደ አሦር ይወሰዳል።+ ኤፍሬም ውርደት ይከናነባል፤እስራኤልም በተከተለው ምክር የተነሳ ያፍራል።+
49 “ይሖዋ ቋንቋውን የማትረዳውን+ በሩቅ ያለን አንድ ብሔር ከምድር ጫፍ አስነስቶ ያመጣብሃል፤+ እሱም እንደ ንስር ተምዘግዝጎ ይወርድብሃል፤+ 50 ይህ ብሔር ለሽማግሌ የማያዝን ወይም ለወጣት የማይራራ ፊቱ የሚያስፈራ ብሔር ነው።+
29 በእስራኤል ንጉሥ በፋቁሄ ዘመን የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር+ ወረራ በማካሄድ ኢዮንን፣ አቤልቤትማዓካን፣+ ያኖአህን፣ ቃዴሽን፣+ ሃጾርን፣ ጊልያድን+ እንዲሁም ገሊላን ይኸውም መላውን የንፍታሌም+ ምድር ያዘ፤ ነዋሪዎቹንም በግዞት ወደ አሦር ወሰደ።+
6 ሆሺአ በነገሠ በዘጠነኛው ዓመት የአሦር ንጉሥ ሰማርያን ያዘ።+ ከዚያም የእስራኤልን ሕዝብ ወደ አሦር በግዞት+ በመውሰድ በሃላህ፣ በጎዛን+ ወንዝ አጠገብ በምትገኘው በሃቦርና በሜዶናውያን ከተሞች አሰፈራቸው።+
20 “በዚያም ቀን ይሖዋ በወንዙ* አካባቢ ከሚገኘው ቦታ በተከራየው ምላጭ ይኸውም በአሦር ንጉሥ+ አማካኝነት ራሱንና የእግሩን ፀጉር ይላጨዋል፤ ጢሙንም ሙልጭ አድርጎ ያስወግደዋል።
5 “የቁጣዬ በትር የሆነውንና+ውግዘቴን የምገልጽበትን ዱላ በእጁ የያዘውንአሦራዊ+ ተመልከት! 6 ከሃዲ በሆነው ብሔር ላይ፣እጅግ ባስቆጣኝም ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፤+ብዙ ምርኮ እንዲወስድ፣ ብዙ ሀብት እንዲዘርፍናሕዝቡን በጎዳናዎች ላይ እንዳለ ጭቃ እንዲረጋግጥ አዘዋለሁ።+