የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 1 ሳሙኤል 19
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

1 ሳሙኤል የመጽሐፉ ይዘት

      • ሳኦል ዳዊትን ይበልጥ ጠላው (1-13)

      • ዳዊት ከሳኦል አመለጠ (14-24)

1 ሳሙኤል 19:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:9፤ ምሳሌ 27:4

1 ሳሙኤል 19:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:1፤ ምሳሌ 18:24

1 ሳሙኤል 19:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 20:9, 13፤ ምሳሌ 17:17

1 ሳሙኤል 19:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 22:14

1 ሳሙኤል 19:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሱን በእጁ ይዞ።”

  • *

    ወይም “መዳን አስገኘ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 17:49
  • +1ሳሙ 20:32

1 ሳሙኤል 19:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 16:21፤ 18:2, 13

1 ሳሙኤል 19:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 16:14
  • +1ሳሙ 18:10, 11

1 ሳሙኤል 19:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍስህ እንድታመልጥ ካላደረግክ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 59:በመዝሙሩ አናት ላይ የሚገኘው መግለጫ፤ 59:3

1 ሳሙኤል 19:13

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የቤት ውስጥ አምላኩን፤ ጣዖቱን።”

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    6/1/2004፣ ገጽ 29

1 ሳሙኤል 19:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:9

1 ሳሙኤል 19:16

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የቤት ውስጥ አምላኩን፤ ጣዖቱን።”

1 ሳሙኤል 19:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 18:29

1 ሳሙኤል 19:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 7:15, 17
  • +1ሳሙ 20:1

1 ሳሙኤል 19:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 19:18

1 ሳሙኤል 19:24

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከውስጥ በለበሰው ልብስ ብቻ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 10:11

ተዛማጅ ሐሳብ

1 ሳሙ. 19:11ሳሙ 18:9፤ ምሳሌ 27:4
1 ሳሙ. 19:21ሳሙ 18:1፤ ምሳሌ 18:24
1 ሳሙ. 19:31ሳሙ 20:9, 13፤ ምሳሌ 17:17
1 ሳሙ. 19:41ሳሙ 22:14
1 ሳሙ. 19:51ሳሙ 17:49
1 ሳሙ. 19:51ሳሙ 20:32
1 ሳሙ. 19:71ሳሙ 16:21፤ 18:2, 13
1 ሳሙ. 19:91ሳሙ 16:14
1 ሳሙ. 19:91ሳሙ 18:10, 11
1 ሳሙ. 19:11መዝ 59:በመዝሙሩ አናት ላይ የሚገኘው መግለጫ፤ 59:3
1 ሳሙ. 19:151ሳሙ 18:9
1 ሳሙ. 19:171ሳሙ 18:29
1 ሳሙ. 19:181ሳሙ 7:15, 17
1 ሳሙ. 19:181ሳሙ 20:1
1 ሳሙ. 19:221ሳሙ 19:18
1 ሳሙ. 19:241ሳሙ 10:11
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
1 ሳሙኤል 19:1-24

አንደኛ ሳሙኤል

19 በኋላም ሳኦል፣ ዳዊት እንዲገደል ማሰቡን ለልጁ ለዮናታንና ለአገልጋዮቹ በሙሉ ነገራቸው።+ 2 የሳኦል ልጅ ዮናታን ዳዊትን በጣም ይወደው+ ስለነበር ዳዊትን እንዲህ አለው፦ “አባቴ ሳኦል ሊገድልህ ይፈልጋል። ስለዚህ እባክህ ጠዋት ላይ ተጠንቀቅ፤ ወደ አንድ ሰዋራ ቦታም ሄደህ ተሸሽገህ ቆይ። 3 እኔም እወጣና አንተ ባለህበት ሜዳ ከአባቴ አጠገብ እቆማለሁ። ከእሱም ጋር ስለ አንተ እነጋገራለሁ፤ የሆነ ነገር እንዳለ ከተረዳሁ እነግርሃለሁ።”+

4 በመሆኑም ዮናታን ለአባቱ ለሳኦል ስለ ዳዊት መልካም ነገር ነገረው።+ እንዲህም አለው፦ “ንጉሡ በአገልጋዩ በዳዊት ላይ ኃጢአት አይሥራ፤ ምክንያቱም እሱ በአንተ ላይ የሠራው ኃጢአት የለም፤ ያደረገልህም ነገር ቢሆን ለአንተ የሚበጅ ነው። 5 ሕይወቱን አደጋ ላይ ጥሎ* ፍልስጤማዊውን መታ፤+ ይሖዋም ለመላው እስራኤል ታላቅ ድል አጎናጸፈ።* አንተም ይህን አይተህ በጣም ተደስተህ ነበር። ታዲያ ያለምንም ምክንያት ዳዊትን በመግደል በንጹሕ ሰው ደም ላይ ለምን ኃጢአት ትሠራለህ?”+ 6 ሳኦልም የዮናታንን ቃል ሰማ፤ እሱም “ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ ዳዊት አይገደልም” ሲል ማለ። 7 ከዚያም ዮናታን ዳዊትን ጠርቶ ሁሉንም ነገር ነገረው። ስለዚህ ዮናታን ዳዊትን ወደ ሳኦል አመጣው፤ እሱም እንደቀድሞው ሳኦልን ማገልገሉን ቀጠለ።+

8 ከጊዜ በኋላ ሌላ ጦርነት ተነሳ፤ ዳዊትም ወጥቶ ከፍልስጤማውያን ጋር ተዋጋ፤ ክፉኛም ጨፈጨፋቸው፤ እነሱም ከፊቱ ሸሹ።

9 ሳኦል ጦሩን ይዞ ቤቱ ውስጥ ተቀምጦ ሳለ ከይሖዋ የመጣ መጥፎ መንፈስ ወረደበት፤+ በዚህ ጊዜ ዳዊት በገና እየደረደረ ነበር።+ 10 ሳኦልም ዳዊትን በጦሩ ከግድግዳው ጋር ሊያጣብቀው ሞከረ፤ ዳዊት ግን ከሳኦል ፊት ዞር በማለቱ ጦሩ ግድግዳው ላይ ተሰካ። ዳዊትም በዚያ ሌሊት ሸሽቶ አመለጠ። 11 በኋላም ሳኦል የዳዊትን ቤት ከበው በንቃት በመጠባበቅ ጠዋት ላይ እንዲገድሉት መልእክተኞችን ላከ፤+ ሆኖም የዳዊት ሚስት ሜልኮል “ዛሬ ሌሊት ካላመለጥክ* ነገ ትገደላለህ” አለችው። 12 ሜልኮልም ዳዊት ሸሽቶ እንዲያመልጥ ወዲያውኑ በመስኮት አሾልካ አወረደችው። 13 ከዚያም የተራፊም ቅርጹን* ወስዳ አልጋው ላይ አጋደመች፤ በራስጌውም ከፍየል ፀጉር የተሠራ እንደ መረብ ያለ ጨርቅ አደረገች፤ በልብስም ሸፈነችው።

14 ሳኦልም ዳዊትን እንዲይዙት መልእክተኞችን ላከ፤ እሷ ግን “አሞታል” አለቻቸው። 15 በመሆኑም ሳኦል ዳዊትን እንዲያዩት መልእክተኞቹን ላከ፤ እነሱንም “ዳዊትን እንድገድለው በአልጋው ላይ እንዳለ አምጡልኝ” አላቸው።+ 16 መልእክተኞቹም ሲገቡ አልጋው ላይ ያገኙት የተራፊም ቅርጹን* ነበር፤ በራስጌውም ከፍየል ፀጉር የተሠራ እንደ መረብ ያለ ጨርቅ ነበር። 17 ሳኦልም ሜልኮልን “እንዲህ ያታለልሽኝና ጠላቴ+ ሸሽቶ እንዲያመልጥ ያደረግሽው ለምንድን ነው?” አላት። ሜልኮልም “‘እንዳመልጥ እርጂኝ፣ አለዚያ እገድልሻለሁ!’ አለኝ” አለችው።

18 ዳዊትም ሸሽቶ አመለጠ፤ በራማ+ ወደሚገኘው ወደ ሳሙኤልም መጣ። ሳኦል ያደረገበትንም ነገር ሁሉ ነገረው። ከዚያም እሱና ሳሙኤል ሄደው በናዮት+ መኖር ጀመሩ። 19 ከጊዜ በኋላም ሳኦል “ዳዊት እኮ ያለው በራማ በምትገኘው በናዮት ነው!” የሚል ወሬ ደረሰው። 20 ሳኦልም ዳዊትን እንዲይዙት ወዲያውኑ መልእክተኞችን ላከ። የሳኦል መልእክተኞችም አረጋውያን የሆኑት ነቢያት ትንቢት ሲናገሩ፣ ሳሙኤል ደግሞ እንደ መሪያቸው ሆኖ ቆሞ ሲያዩ የአምላክ መንፈስ ወረደባቸው፤ እነሱም እንደ ነቢያት ያደርጋቸው ጀመር።

21 ይህን ለሳኦል በነገሩት ጊዜ ወዲያውኑ ሌሎች መልእክተኞችን ላከ፤ እነሱም እንደ ነቢያት ያደርጋቸው ጀመር። በመሆኑም ሳኦል ለሦስተኛ ጊዜ መልእክተኞችን ላከ፤ እነሱም እንደ ነቢያት ያደርጋቸው ጀመር። 22 በመጨረሻም እሱ ራሱ ወደ ራማ ሄደ። በሰኩ ወደሚገኘው ትልቅ የውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ እንደደረሰም “ለመሆኑ ሳሙኤልና ዳዊት የት ናቸው?” ሲል ጠየቀ። እነሱም “በራማ ባለችው በናዮት+ ይገኛሉ” ብለው መለሱለት። 23 ሳኦልም በራማ ወደምትገኘው ወደ ናዮት እየሄደ ሳለ የአምላክ መንፈስ በእሱም ላይ ወረደበት፤ እሱም በራማ ወደምትገኘው ወደ ናዮት እስኪደርስ ድረስ እንደ ነቢይ አደረገው። 24 ልብሱንም አወለቀ፤ በሳሙኤልም ፊት እንደ ነቢይ አደረገው፤ ቀኑንና ሌሊቱን ሙሉ ራቁቱን* ሆኖ በዚያ ተጋደመ። እነሱም “ሳኦልም ከነቢያቱ አንዱ ነው እንዴ?”+ ያሉት በዚህ የተነሳ ነው።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ