ዓመታዊ ስብሰባ
ጥቅምት 2, 1993
የፔንሲልቫንያ የመጠበቂያ ግንብ የመጽሐፍ ቅዱስና ትራክት ማኅበር አባሎች ዓመታዊ ስብሰባ በኬኔዲ ቡልቫርድ 2932 ጀርሲ ሲቲ፣ ኒው ጀርሲ በሚገኘው የይሖዋ ምስክሮች የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ጥቅምት 2, 1993 ይካሄዳል። በመጀመሪያው የማኅበሩ አባላት ብቻ የሚገኙበት ስብሰባ በ3:30 ይጀምራል። ከዚያ በኋላ አጠቃላዩ ዓመታዊ ስብሰባው በ4:00 ሰዓት ይጀምራል።
የማኅበሩ አባላት ከነሐሴ 1 በኋላ የሚላክላቸው ተከታታይ ደብዳቤና መልዕክት እንዲደርሳቸው ካለፈው ዓመት ወዲህ ቋሚ አድራሻቸውን ለውጠው ከሆነ አሁኑኑ ለማኅበሩ ጸሐፊ ቢሮ ማስታወቅ ይኖርባቸዋል።
ለአባላቱ የሚላከው የዓመታዊው ስብሰባ የማስታወቂያና የውክልና ደብዳቤ ለማኅበሩ ጸሐፊ ቢሮ ከነሐሴ 15 ቀን በፊት እንዲደርስ ሳይዘገይ መመለስ ይኖርበታል። እያንዳንዱ አባል በስብሰባው ላይ ይገኝ እንደሆነና እንዳልሆነ በመግለጽ የውክልናውን ሰነድ ወዲያውኑ አጠናቅቆ መሙላትና መመለስ ይኖርበታል። በእያንዳንዱ ሰነድ ላይ የሚሰጠው መረጃ የማያሻማ መሆን ይገባዋል። ምክንያቱም በስብሰባው ላይ የሚገኙትንና የማይገኙትን ለማወቅ የሚቻለው በዚህ መረጃ አማካኝነት ብቻ ነው።
አጠቃላዩ ስብሰባ የማኅበሩን የአሠራር ጉዳዮችንና ሪፖርቶችን ጨምሮ በ7:00 ሰዓት ላይ ወይም ከዚያ ትንሽ ዘግየት ብሎ ይጠናቀቃል። ከሰዓት በኋላ ስብሰባ አይኖርም። ያለው ቦታ የተወሰነ ስለሆነ ወደ ስብሰባው መግባት የሚፈቀደው ቲኬት ለያዙ ብቻ ነው። የስብሰባውን ሂደት ከስልክ መስመሮች ጋር አገናኝቶ ለሌሎች አካባቢዎች ለማስተላለፍ የተደረገ ምንም ዓይነት ዝግጅት የለም።