ዓመታዊ ስብሰባ—ጥቅምት 3, 1992
የፔንሲልቫንያ የመጠበቂያ ግንብ መጽሐፍ ቅዱስና ትናንሽ ጽሑፎች ማህበር ዓመታዊ ስብሰባ በኬኔዲ ቡልቫርድ 2932 ጀርሲ ሲቲ፣ ኒው ጀርሲ በሚገኘው የይሖዋ ምሥክሮች የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ጥቅምት 3, 1992 ይካሄዳል። በመጀመሪያ በ3:30 ላይ አባላቱ ብቻ ስብሰባ ያደርጋሉ። ከዚያም በ4:00 ላይ አጠቃላዩ ዓመታዊ ስብሰባ ይደረጋል።
የኮርፖሬሽኑ አባላት ቋሚ የሆኑት ደብዳቤዎችና የውክልና ካርዳቸው ከነሐሴ 1, 1992 በኋላ ባጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ባለፉት ዓመታት ባላቸው የፖስታ አድራሻቸው ላይ የተደረገ ለውጥ ካለ አሁኑኑ ለጸሐፊው ቢሮ ማስታወቅ ይኖርባቸዋል።
ዓመታዊውን ስብሰባ ከሚያስታውቀው ደብዳቤ ጋር ለአባላቱ የሚላኩት የውክልና ሰነዶች ከነሐሴ 15, 1992 በፊት ተመልሰው ወደ ማህበሩ ጸሐፊ ቢሮ መድረስ አለባቸው። እያንዳንዱ አባል በስብሰባው ላይ ይገኝ እንደሆነና እንዳልሆነ በመግለጽ የውክልና ሰነዱን ወዲያውኑ አጠናቅቆ መመለስ ይኖርበታል። እያንዳንዱ ሰነድ ላይ የሚሰጠው መረጃ የተወሰነ መሆን አለበት። ምክንያቱም ማን በስብሰባው ላይ እንደሚገኝና እንደማይገኝ የሚወሰነው ከዚህ በሚገኘው መረጃ ነው።
አጠቃላይ ስብሰባው የሒሳብ ሪፖርቶችን ጨምሮ በ7:00 ላይ ወይም ከዚያ ትንሽ ዘግየት ብሎ ይጠናቀቃል። ከሰዓት በኋላ ስብሰባ አይኖርም። ያለው ቦታ የተወሰነ ስለሆነ ወደ ስብሰባው ለመምጣት የሚፈቀደው ቲኬት ለያዙ ብቻ ነው። ዓመታዊ ስብሰባውን ከስልክ መስመሮች ጋር አገናኝቶ ለሌሎች ለማስተላለፍ ምንም ዓይነት ዝግጅት አይደረግም።