ነሐሴ 10 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
ነሐሴ 10 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 61 እና ጸሎት
የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
bt ምዕ. 22 ከአን. 15-21 (30 ደቂቃ)
ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 1 ነገሥት 21-22 (8 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ 1 ነገሥት 22:13-23 (3 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ወደ አምላክ መቅረብ የምትችለው እንዴት ነው?—nwt ገጽ 32 አን. 1-4 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ ደሊላ—ጭብጥ፦ የገንዘብ ፍቅር ክህደት ወደ መፈጸም ይመራል—w12 4/15 ገጽ 9 አን. 4 እና 7 (5 ደቂቃ)
የአገልግሎት ስብሰባ፦
የወሩ ጭብጥ፦ “እኔና ቤተሰቤ ግን ይሖዋን እናገለግላለን።” —ኢያሱ 24:15
10 ደቂቃ፦ “እኔና ቤተሰቤ ግን ይሖዋን እናገለግላለን።” በወሩ ጭብጥ ላይ ተመሥርቶ የሚቀርብ ንግግር። ዘዳግም 6:6, 7ን፣ ኢያሱ 24:15ንና ምሳሌ 22:6ን አንብብና እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል አብራራ። የቤተሰቡን መንፈሳዊነት በተመለከተ ዋነኛ ኃላፊነት ያለበት ባል ወይም አባት እንደሆነ ጎላ አድርገህ ግለጽ። የይሖዋ ድርጅት ቤተሰቦችን ለመርዳት ያደረጋቸውን የተለያዩ ዝግጅቶች ተናገር። በዚህ ወር በአገልግሎት ስብሰባ ላይ ከሚቀርቡት ክፍሎች አንዳንዶቹን ጥቀስ፤ እንዲሁም ከወሩ ጭብጥ ጋር ያላቸውን ተያያዥነት ግለጽ።
20 ደቂቃ፦ “በአገልግሎት ረገድ ክህሎታችንን ማዳበር—አዲሶችን ማሠልጠን።” በውይይት የሚቀርብ። ወላጆች ልጆቻቸው መንፈሳዊ እድገት እንዲያደርጉ ለመርዳት በዚህ ክፍል ውስጥ የቀረቡትን ነጥቦች እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚችሉ አድማጮችን ጠይቅ። አንድ አባት ከትንሽ ልጁ (ሴት ልጁም ልትሆን ትችላለች) ጋር በአገልግሎት የሚጠቀሙበትን መግቢያ ሲለማመዱ የሚያሳይ ሠርቶ ማሳያ እንዲቀርብ አድርግ።
መዝሙር 93 እና ጸሎት