የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb25 መስከረም ገጽ 10-11
  • ከጥቅምት 6-12

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ከጥቅምት 6-12
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2025
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2025
mwb25 መስከረም ገጽ 10-11

ከጥቅምት 6-12

መክብብ 5–6

መዝሙር 42 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)

ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት

የተወሰኑ እስራኤላውያን በአንዲት ከተማ በር አቅራቢያ አንድን ካህን ሲያዳምጡ። ካህኑ ጥቅልል ይዟል።

አንድ ካህን ሕጉን ሲያብራራ የተወሰኑ እስራኤላውያን በጥሞና ሲያዳምጡት

1. ታላቁን አምላካችንን በጥልቅ እንደምናከብር ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?

(10 ደቂቃ)

በስብሰባዎች ላይ በጥሞና በማዳመጥ እንዲሁም ለአለባበሳችንና ለአጋጌጣችን ትኩረት በመስጠት አክብሮት እናሳያለን (መክ 5:1፤ w08 8/15 15-16 አን. 17-18)

በሕዝብ ፊት የምናቀርበው ጸሎት ቃላት የበዛበት ሳይሆን በሚገባ የታሰበበትና አክብሮት የሚንጸባረቅበት እንዲሆን እናደርጋለን (መክ 5:2፤ w09 11/15 11 አን. 21)

ራሳችንን ስንወስን የገባነውን ቃል እንጠብቃለን (መክ 5:4-6፤ w17.04 6 አን. 12)

የተወሰኑ እስራኤላውያን በአንዲት ከተማ በር አቅራቢያ አንድን ካህን ሲያዳምጡ። ካህኑ ጥቅልል ይዟል።

2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች

(10 ደቂቃ)

  • መክ 5:8—ኢፍትሐዊ ድርጊት ሲፈጸምብን ይህ ጥቅስ የሚያጽናናን እንዴት ነው? (w20.09 31 አን. 3-5)

  • ከዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ምን መንፈሳዊ ዕንቁዎች አግኝታችኋል?

3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ

(4 ደቂቃ) መክ 5:1-17 (th ጥናት 12)

በአገልግሎት ውጤታማ ለመሆን ተጣጣር

4. ውይይት መጀመር

(1 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። ግለሰቡ መከራከር ጀመረ። (lmd ምዕራፍ 4 ነጥብ 5)

5. ውይይት መጀመር

(2 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። lmd ተጨማሪ መረጃ ሀ ላይ ከሚገኙት “ለማስተማር የምንጓጓቸው እውነቶች” መካከል አንዱን አካፍል። (lmd ምዕራፍ 1 ነጥብ 3)

6. ተመላልሶ መጠየቅ

(3 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። በማስተማሪያ መሣሪያዎቻችን ውስጥ የሚገኝ አንድ ቪዲዮ ተጠቀም። (lmd ምዕራፍ 7 ነጥብ 3)

7. ደቀ መዛሙርት ማድረግ

(5 ደቂቃ) lff ምዕራፍ 17 ማስተዋወቂያ እና ነጥብ 1-3 (lmd ምዕራፍ 11 ነጥብ 3)

ክርስቲያናዊ ሕይወት

መዝሙር 160

8. “ለማስተማር የምንጓጓቸው እውነቶች” የተባለውን ክፍል እየተጠቀማችሁበት ነው?

(15 ደቂቃ) ውይይት።

ከቤት ወደ ቤት እያገለገሉ ያሉ አንድ ባልና ሚስት ለአንድ ወጣት ጥቅስ ሲያነቡለት።

ሰዎችን ውደዱ—ደቀ መዛሙርት አድርጉ የተባለው ብሮሹር ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ውይይት የማድረግ ችሎታችንን እንድናሻሽል እየረዳን ነው። ተጨማሪ መረጃ ሀ የተዘጋጀው ከሰዎች ጋር ውይይት ስናደርግ መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን ለማስተዋወቅ እንዲረዳን ታስቦ ነው። (ዕብ 4:12) “ለማስተማር የምንጓጓቸው እውነቶች” በሚለው ሥር ያሉትን ዘጠኝ ርዕሰ ጉዳዮች በደንብ ታውቋቸዋላችሁ?

  • ከሰዎች ጋር ስንወያይ ተስማሚ ጊዜ መርጠን አንድን መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ማስተዋወቅ የምንችለው እንዴት ነው?—lmd ተጨማሪ መረጃ ሀ

  • በክልላችሁ ውስጥ ይበልጥ ውጤታማ ሆነው ያገኛችኋቸው ርዕሰ ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው?

  • በተጨማሪ መረጃ ሀ ውስጥ ካሉት ጥቅሶች ጋር በደንብ ለመተዋወቅ ምን ማድረግ ትችላላችሁ?

ግብ፦

በተጨማሪ መረጃ ሀ ውስጥ ላለው ለእያንዳንዱ ርዕሰ ጉዳይ ቢያንስ አንድ ጥቅስ ለማስታወስ ጥረት አድርጉ። በክልላችሁ ውስጥ ይበልጥ ውጤታማ ከሆኑት ጀምሩ።

እነዚህን ጥቅሶች በአገልግሎት ላይ በተጠቀምንባቸው መጠን ይበልጥ እየለመድናቸው እንሄዳለን። ይሁንና እነዚህን ጥቅሶች አዘውትረን መጠቀም እንድንችል በመጀመሪያ በክልላችን ውስጥ ያሉትን ሰዎች ማግኘት አለብን።

‘ብረት ብረትን ይስላል’—ለብዙ ሰዎች መመሥከር የተባለውን ቪዲዮ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦

  • በክልላችን ውስጥ ብዙ ሰዎችን ለማግኘት ምን ሊረዳን ይችላል?

9. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

(30 ደቂቃ) lfb ትምህርት 24-25

የመደምደሚያ ሐሳብ (3 ደቂቃ) | መዝሙር 34 እና ጸሎት

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ