የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 43 ገጽ 104
  • ንጉሥ ዳዊት የሠራው ኃጢአት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ንጉሥ ዳዊት የሠራው ኃጢአት
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በዳዊት ቤት ውስጥ ችግር ተፈጠረ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • በሕይወታችሁ የሚያጋጥሟችሁን ለውጦች ለመቋቋም በአምላክ መንፈስ ታመኑ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2004
  • መናዘዝ ፈውስ ያስገኛል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • ‘የተሰበረና የተዋረደ ልብ’ ያላቸው ሰዎች ምሕረት በሚፈልጉበት ጊዜ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 43 ገጽ 104
ነቢዩ ናታን ለንጉሥ ዳዊት ተግሣጽ ሲሰጠው

ትምህርት 43

ንጉሥ ዳዊት የሠራው ኃጢአት

ሳኦል ከሞተ በኋላ ዳዊት ንጉሥ ሆነ። በወቅቱ ዳዊት 30 ዓመቱ ነበር። ለተወሰኑ ዓመታት ንጉሥ ሆኖ ከገዛ በኋላ አንድ ከባድ ስህተት ሠራ። አንድ ቀን ምሽት ላይ በቤተ መንግሥቱ ሰገነት ላይ ሆኖ አንዲት ቆንጆ ሴት አየ። ዳዊት ስለ ሴትየዋ ማንነት ሲጠይቅ ስሟ ቤርሳቤህ እንደሆነና ኦርዮ የሚባል አንድ ወታደር ሚስት እንደሆነች ነገሩት። ዳዊት ቤርሳቤህን ወደ ቤተ መንግሥቱ አስመጣት። ከዚያም አብሯት ተኛ፤ እሷም አረገዘች። ዳዊት ያደረገውን ነገር ለመደበቅ ሞከረ። ለጦር አዛዡ መልእክት ልኮ ኦርዮን ውጊያው ላይ ፊት ለፊት እንዲያሰልፈውና ሌሎቹ ወታደሮች ጥለውት እንዲሸሹ እንዲያደርግ ነገረው። ኦርዮ በጦርነቱ ከተገደለ በኋላ ዳዊት ቤርሳቤህን አገባት።

ንጉሥ ዳዊት ኃጢአቱ ይቅር እንዲባልለት ሲጸልይ

ሆኖም ይሖዋ የተፈጸመውን መጥፎ ድርጊት በሙሉ ተመልክቶ ነበር። ታዲያ ምን ያደርግ ይሆን? ይሖዋ ነቢዩ ናታንን ወደ ዳዊት ላከው። ናታን ዳዊትን እንዲህ አለው፦ ‘አንድ ሀብታም ሰውና አንድ ድሃ ሰው ነበሩ፤ ሀብታሙ ሰው ብዙ በጎች ነበሩት፤ ድሃው ግን የነበረችው አንዲት ትንሽ የበግ ጠቦት ብቻ ነበረች። እሷንም በጣም ይወዳት ነበር። ሀብታሙ ሰው ድሃው የነበረችውን አንዲት ጠቦት ወሰደበት።’ በዚህ ጊዜ ዳዊት በጣም ተናዶ ‘ያ ሀብታም ሰው መሞት ይገባዋል!’ አለ። ከዚያም ናታን ዳዊትን ‘ያ ሀብታም ሰው አንተ ነህ!’ አለው። ዳዊት በጣም አዘነ፤ ከዚያም ጥፋቱን በማመን ‘በይሖዋ ላይ ኃጢአት ሠርቻለሁ’ አለ። ይህ ኃጢአት በዳዊትና በቤተሰቡ ላይ ብዙ ችግር አምጥቷል። ይሖዋ ዳዊትን የቀጣው ቢሆንም ዳዊት ሐቀኛና ትሑት በመሆኑ በሕይወት እንዲኖር ፈቅዶለታል።

ዳዊት ለይሖዋ ቤተ መቅደስ መገንባት ፈልጎ ነበር፤ ይሖዋ ግን ቤተ መቅደሱን እንዲገነባ የመረጠው ልጁን ሰለሞንን ነበር። ዳዊት ቤተ መቅደሱን ለመገንባት የሚያስፈልጉትን ነገሮች ለሰለሞን ማዘጋጀት ጀመረ፤ እንዲህም አለ፦ ‘የይሖዋ ቤተ መቅደስ በጣም ውብ መሆን አለበት። ሰለሞን ገና ልጅ ነው፤ ስለዚህ የሚያስፈልገውን ነገር በማዘጋጀት እረዳዋለሁ።’ ዳዊት ለቤተ መቅደሱ ግንባታ የሚሆን በጣም ብዙ ገንዘብ ሰጠ። እንዲሁም ጥሩ ችሎታ ያላቸው ሠራተኞችን አዘጋጀለት። ወርቅና ብር አሰባሰበ፤ ከጢሮስና ከሲዶናም የአርዘ ሊባኖስ እንጨት አስመጣ። ዳዊት መሞቻው ሲቃረብ ለሰለሞን ቤተ መቅደሱ እንዴት እንደሚሠራ የሚያሳይ ንድፍ ሰጠው። እንዲህም አለው፦ ‘ይሖዋ እነዚህን ነገሮች በጽሑፍ እንዳሰፍርልህ ነግሮኛል። ይሖዋ ይረዳሃል። አትፍራ። ደፋር ሁን፤ ሥራውን በትጋት አከናውን።’

ዳዊት ስለ ቤተ መቅደሱ ንድፍ ከወጣቱ ሰለሞን ጋር ሲነጋገር

“የሠራውን በደል የሚሸፋፍን አይሳካለትም፤ የሚናዘዝና የሚተወው ሁሉ ግን ምሕረት ያገኛል።”—ምሳሌ 28:13

ጥያቄ፦ ዳዊት የሠራው ኃጢአት ምንድን ነው? ዳዊት ልጁን ሰለሞንን ለመርዳት ምን አደረገ?

2 ሳሙኤል 5:3, 4, 10፤ 7:1-16፤ 8:1-14፤ 11:1–12:14፤ 1 ዜና መዋዕል 22:1-19፤ 28:11-21፤ መዝሙር 51:1-19

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ