ዓመታዊ ስብሰባ—ጥቅምት 5, 1991
የፔንስልቫንያው የመጽሐፍ ቅዱስና የትንንሽ ጽሑፎች ማኅበር ዓመታዊ ስብሰባ በኒው ጀርሲ፣ በጀርሲ ከተማ ውስጥ በ2932 ኬኔዲ ቦልቫርድ በሚገኘው የይሖዋ ምስክሮች የመሰብሰቢያ አዳራሽ ጥቅምት 5, 1991 ይደረጋል። የመጀመሪያው የአባሎች ስብሰባ በ3:30 ይሰበሰባል። ከዚያም በ4 ሰዓት አጠቃላዩ ዓመታዊ ስብሰባ ይደረጋል።
የኮርፖሬሽኑ አባሎች የተለመደው የማስታወሻና የተወካዮች ደብዳቤ በጊዜው ይደርሳቸው ዘንድ ባለፈው ዓመት ውስጥ የአድራሻ ለውጥ አድርገው ከሆነ ለጸሐፊው ቢሮ ማስታወቅ ይኖርባቸዋል።
ከዓመታዊው ስብሰባ ማስታወሻ ጋር ለአባሎቹ የሚላኩት የውክልና ደብዳቤዎች ወደ ጸሐፊው ቢሮ እንዲደርሱ ከነሐሴ 15 ቀን በፊት መመለስ ይኖርባቸዋል። እያንዳንዱ አባል ራሱ በስብሰባው ላይ በግል ይገኝ እንደሆነና እንዳልሆነ በመግለጽ ውክልናውን አሟልቶ ወዲያውኑ መመለስ ይኖርበታል። በግል ሊገኝ የሚችለው ሰው ማን መሆኑን ለመወሰን የሚቻለው በዚህ በመሆኑ በእያንዳንዱ ደብዳቤ ላይ የተሰጠው መረጃ በዚህ ነጥብ ላይ ቁርጥ ያለ መሆን ይኖርበታል።
አጠቃላይ የፕሮግራሙ ጊዜ ይኸውም መደበኛው የሥራ ጉዳይና ሪፖርት የማቅረቡ ስብሰባ በ7 ሰዓት ወይም ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ይፈጸማል ተብሎ ይጠበቃል። የከሰዓት በኋላ ፕሮግራም አይኖርም። ያለው ቦታ የተወሰነ በመሆኑ ለመግባት የሚፈቀደው በቲኬት ብቻ ይሆናል። ዓመታዊውን ስብሰባ በስልክ መስመሮች ወደ ሌሎች አስተዳደሮች ለማስተላለፍ ምንም ዝግጅት አይደረግም።