መዝሙር
ለሙዚቀኞች ቡድን መሪ። ማስኪል።* የዳዊት መዝሙር፤ ኤዶማዊው ዶይቅ ወደ ሳኦል ሄዶ፣ ዳዊት ወደ አሂሜሌክ ቤት መጥቶ እንደነበር በነገረው ጊዜ።+
52 አንተ ኃያል፣ መጥፎ በሆነው ተግባርህ የምትኩራራው ለምንድን ነው?+
የአምላክ ታማኝ ፍቅር ዘላቂ እንደሆነ አታውቅም?+
3 መልካም ከሆነው ነገር ይልቅ ክፋትን፣
ትክክል የሆነውን ነገር ከመናገር ይልቅ ሐሰትን ትወዳለህ። (ሴላ)
4 አንተ አታላይ ምላስ!
ጎጂ ቃልን ሁሉ ትወዳለህ።
8 እኔ ግን በአምላክ ቤት እንዳለ የለመለመ የወይራ ዛፍ እሆናለሁ፤
ለዘላለም በአምላክ ታማኝ ፍቅር እታመናለሁ።+