የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘሌዋውያን 26:6
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 6 በምድሪቱ ሰላም አሰፍናለሁ፤+ እናንተም ማንም ሳያስፈራችሁ ትተኛላችሁ፤+ እኔም አደገኛ አውሬዎች በምድሪቱ እንዳይኖሩ አደርጋለሁ፤ በምድራችሁም የጦርነት ሰይፍ አያልፍም።

  • ኢሳይያስ 11:6-9
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  6 ተኩላ ከበግ ጠቦት ጋር የሚቀመጥበት ጊዜ ይኖራል፤+

      ነብርም ከፍየል ግልገል ጋር ይተኛል፤

      ጥጃ፣ አንበሳና* የሰባ ከብት አብረው ይሆናሉ፤*+

      ትንሽ ልጅም ይመራቸዋል።

       7 ላምና ድብ አብረው ይበላሉ፤

      ልጆቻቸውም አብረው ይተኛሉ።

      አንበሳ እንደ በሬ ገለባ ይበላል።+

       8 ጡት የሚጠባ ሕፃንም በእባብ* ጉድጓድ ላይ ይጫወታል፤

      ጡት የጣለውም ሕፃን እጁን በመርዘኛ እባብ ጎሬ ላይ ያደርጋል።

       9 በተቀደሰው ተራራዬ ሁሉ ላይ

      ምንም ዓይነት ጉዳት ወይም ጥፋት አያደርሱም፤+

      ምክንያቱም ውኃ ባሕርን እንደሚሸፍን

      ምድርም በይሖዋ እውቀት ትሞላለች።+

  • ኢሳይያስ 35:9
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  9 በዚያ አንበሳ አይኖርም፤

      አዳኝ አራዊትም ወደዚያ አይወጡም።

      አንዳቸውም በዚያ አይገኙም፤+

      የተቤዡት ብቻ በዚያ ይሄዳሉ።+

  • ኢሳይያስ 65:25
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 25 ተኩላና የበግ ግልገል በአንድነት ይበላሉ፤

      አንበሳ እንደ በሬ ገለባ ይበላል፤+

      የእባብም መብል አፈር ይሆናል።

      በተቀደሰው ተራራዬ ሁሉ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳትም ሆነ ጥፋት አያደርሱም”+ ይላል ይሖዋ።

  • ሆሴዕ 2:18
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 18 በዚያም ቀን ለእነሱ ጥቅም ስል ከዱር አራዊት፣+

      ከሰማይ ወፎችና መሬት ለመሬት ከሚሳቡ ፍጥረታት ጋር ቃል ኪዳን አደርጋለሁ፤+

      ቀስትን፣ ሰይፍንና ጦርነትን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ፤+

      ያለስጋት እንዲያርፉም* አደርጋለሁ።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ