የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 21:11
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 11 በዱማ* ላይ የተላለፈ ፍርድ፦

      አንዱ ከሴይር ጠርቶኝ እንዲህ አለኝ፦+

      “ጠባቂ ሆይ፣ ስለ ሌሊቱ ምን ትላለህ?

      ጠባቂ ሆይ፣ ስለ ሌሊቱ ምን ትላለህ?”

  • ሕዝቅኤል 25:12-14
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 12 “ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘ኤዶም በቂም በቀል ተነሳስቶ በይሁዳ ቤት ላይ እርምጃ ወስዷል፤ ደግሞም እነሱን በመበቀል ከፍተኛ በደል ፈጽሟል፤+ 13 ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “እጄን በኤዶምም ላይ እዘረጋለሁ፤ ከምድሪቱም ላይ ሰውንም ሆነ ከብትን አጠፋለሁ፤ ባድማም አደርጋታለሁ።+ ከቴማን አንስቶ እስከ ዴዳን ድረስ በሰይፍ ይወድቃሉ።+ 14 ‘በሕዝቤ በእስራኤል እጅ ኤዶምን እበቀላለሁ።+ እነሱም፣ ኤዶም የምወስደውን የበቀል እርምጃ ይቀምስ ዘንድ ቁጣዬንና መዓቴን በኤዶም ላይ ያወርዳሉ’+ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።”’

  • ኢዩኤል 3:19
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 19 ግብፅ ግን ባድማ ትሆናለች፤+

      ኤዶምም በምድራቸው ንጹሕ ደም በማፍሰስ+

      በይሁዳ ሕዝብ ላይ ግፍ ስለፈጸመች+

      ጠፍ ምድረ በዳ ትሆናለች።+

  • አሞጽ 1:11, 12
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 11 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦

      ‘ስለ ሦስቱ የኤዶም ዓመፅ+ ብሎም ስለ አራቱ እጄን አልመልስም፤

      ምክንያቱም የገዛ ወንድሙን በሰይፍ አሳዷል፤+

      ምሕረት ለማሳየትም እንቢተኛ ሆኗል፤

      በቁጣው ያላንዳች ፋታ ይዘነጣጥላቸዋል፤

      አሁንም ቢሆን በእነሱ ላይ ቁጣው አልበረደም።+

      12 በመሆኑም በቴማን+ ላይ እሳት እሰዳለሁ፤

      የቦስራንም የማይደፈሩ ማማዎች ይበላል።’+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ