የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 14
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • አብራም ሎጥን ታደገው (1-16)

      • መልከጼዴቅ አብራምን ባረከው (17-24)

ዘፍጥረት 14:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 10:9, 10
  • +ዘፍ 10:22
  • +ዘፍ 14:17

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    8/15/2001፣ ገጽ 23

ዘፍጥረት 14:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 10:19፤ 13:12
  • +ዘፍ 13:10, 12
  • +ዘዳ 29:23

ዘፍጥረት 14:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “እነዚህ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በዘፍጥረት 14:1 ላይ የተጠቀሱትን ነገሥታት ነው።

  • *

    ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”

  • *

    ሙት ባሕርን ያመለክታል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 14:10
  • +ዘኁ 34:2, 12

ዘፍጥረት 14:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 2:10, 11

ዘፍጥረት 14:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 2:12
  • +ዘፍ 36:8

ዘፍጥረት 14:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 20:1
  • +ዘፍ 36:12፤ 1ሳሙ 15:2
  • +2ዜና 20:2
  • +ዘፍ 10:15, 16

ዘፍጥረት 14:8

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”

ዘፍጥረት 14:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 14:1, 2

ዘፍጥረት 14:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”

ዘፍጥረት 14:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 14:16

ዘፍጥረት 14:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 19:1

ዘፍጥረት 14:13

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በድንኳኖች ውስጥ ይኖር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 14:24
  • +ዘፍ 13:18

ዘፍጥረት 14:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ወንድሙ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 11:27
  • +መሳ 18:29

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    9/1/2009፣ ገጽ 3

    5/15/2004፣ ገጽ 26-27

    8/15/2001፣ ገጽ 23-24

ዘፍጥረት 14:17

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 18:18

ዘፍጥረት 14:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዕብ 7:1, 2
  • +መዝ 110:4፤ ዕብ 6:20
  • +መዝ 83:18፤ ዕብ 5:5, 10

ዘፍጥረት 14:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዕብ 7:4

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የስብሰባው አስተዋጽኦ የማመሣከሪያ ጽሑፎች፣ 9/2019፣ ገጽ 1

ዘፍጥረት 14:21

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳቱን።”

ዘፍጥረት 14:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 14:13

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 14:1ዘፍ 10:9, 10
ዘፍ. 14:1ዘፍ 10:22
ዘፍ. 14:1ዘፍ 14:17
ዘፍ. 14:2ዘፍ 10:19፤ 13:12
ዘፍ. 14:2ዘፍ 13:10, 12
ዘፍ. 14:2ዘዳ 29:23
ዘፍ. 14:3ዘፍ 14:10
ዘፍ. 14:3ዘኁ 34:2, 12
ዘፍ. 14:5ዘዳ 2:10, 11
ዘፍ. 14:6ዘዳ 2:12
ዘፍ. 14:6ዘፍ 36:8
ዘፍ. 14:7ዘኁ 20:1
ዘፍ. 14:7ዘፍ 36:12፤ 1ሳሙ 15:2
ዘፍ. 14:72ዜና 20:2
ዘፍ. 14:7ዘፍ 10:15, 16
ዘፍ. 14:9ዘፍ 14:1, 2
ዘፍ. 14:11ዘፍ 14:16
ዘፍ. 14:12ዘፍ 19:1
ዘፍ. 14:13ዘፍ 14:24
ዘፍ. 14:13ዘፍ 13:18
ዘፍ. 14:14ዘፍ 11:27
ዘፍ. 14:14መሳ 18:29
ዘፍ. 14:172ሳሙ 18:18
ዘፍ. 14:18ዕብ 7:1, 2
ዘፍ. 14:18መዝ 110:4፤ ዕብ 6:20
ዘፍ. 14:18መዝ 83:18፤ ዕብ 5:5, 10
ዘፍ. 14:20ዕብ 7:4
ዘፍ. 14:24ዘፍ 14:13
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 14:1-24

ዘፍጥረት

14 በዚያን ጊዜ የሰናኦር+ ንጉሥ አምራፌል፣ የኤላሳር ንጉሥ አርዮክ፣ የኤላም+ ንጉሥ ኮሎዶጎምር+ እና የጎይም ንጉሥ ቲድአል 2 ከሰዶም+ ንጉሥ ከቤራ፣ ከገሞራ+ ንጉሥ ከቢርሻ፣ ከአድማህ ንጉሥ ከሺንአብ፣ ከጸቦይም+ ንጉሥ ከሸሜበር እና ከቤላ ማለትም ከዞአር ንጉሥ ጋር ጦርነት ገጠሙ። 3 እነዚህ* ሁሉ በሲዲም ሸለቆ*+ ማለትም በጨው ባሕር*+ ሠራዊታቸውን አሰባሰቡ።

4 እነሱም ኮሎዶጎምርን 12 ዓመት አገለገሉት፤ በ13ኛው ዓመት ግን ዓመፁ። 5 ስለሆነም በ14ኛው ዓመት ኮሎዶጎምርና አብረውት የነበሩት ነገሥታት መጥተው ረፋይምን በአስተሮትቃርናይም፣ ዙዚምን በሃም፣ ኤሚምን+ በሻዌቂሪያታይም፣ 6 ሆራውያንን+ ደግሞ ሴይር+ ከሚባለው ተራራቸው አንስቶ በምድረ በዳ እስከሚገኘው እስከ ኤልጳራን ድረስ በሚዘልቀው ስፍራ ድል አደረጓቸው። 7 ከዚያም ቃዴስ+ ወደምትባለው ወደ ኤንሚሽጳጥ ተመልሰው በመምጣት መላውን የአማሌቃውያን+ ግዛትና በሃጻጾንታማር+ ይኖሩ የነበሩትን አሞራውያንን+ ድል አደረጉ።

8 በዚህ ጊዜ የሰዶም ንጉሥ፣ የገሞራ ንጉሥ፣ የአድማህ ንጉሥ፣ የጸቦይም ንጉሥ እንዲሁም የቤላ ማለትም የዞአር ንጉሥ ከእነሱ ጋር ለመዋጋት ሠራዊታቸውን አስተባብረው በሲዲም ሸለቆ* ውስጥ ለጦርነት ተሰለፉ፤ 9 የኤላምን ንጉሥ ኮሎዶጎምርን፣ የጎይምን ንጉሥ ቲድአልን፣ የሰናኦርን ንጉሥ አምራፌልን እንዲሁም የኤላሳርን+ ንጉሥ አርዮክን ለመውጋት ተነሱ፤ አራቱ ነገሥታት ከአምስቱ ጋር ተዋጉ። 10 የሲዲም ሸለቆ* በቅጥራን ጉድጓዶች የተሞላ ነበር፤ የሰዶምና የገሞራ ነገሥታት ሸሽተው ለማምለጥ ሲሞክሩ እነዚህ ጉድጓዶች ውስጥ ወደቁ፤ የቀሩት ደግሞ ወደ ተራራማው አካባቢ ሸሹ። 11 ከዚያም ድል አድራጊዎቹ የሰዶምንና የገሞራን ንብረት በሙሉ እንዲሁም ምግባቸውን ሁሉ ይዘው ሄዱ።+ 12 በተጨማሪም በሰዶም ይኖር የነበረውን የአብራምን የወንድም ልጅ ሎጥን+ ከነንብረቱ ይዘውት ሄዱ።

13 ከዚያም አንድ ያመለጠ ሰው መጥቶ ለዕብራዊው ለአብራም ነገረው። በዚያን ጊዜ አብራም የኤሽኮል እና የአኔር ወንድም በሆነው በአሞራዊው በማምሬ+ ትላልቅ ዛፎች አጠገብ ይኖር* ነበር።+ እነዚህ ሰዎች የአብራም አጋሮች ነበሩ። 14 በዚህ መንገድ አብራም ዘመዱ*+ በምርኮ መወሰዱን ሰማ። ስለሆነም በቤቱ የተወለዱትን 318 የሠለጠኑ አገልጋዮች ሰብስቦ ተነሳ፤ ወራሪዎቹንም ተከትሎ እስከ ዳን+ ድረስ ሄደ። 15 በሌሊትም ሠራዊቱን ከፋፈለ፤ እሱና አገልጋዮቹም በወራሪዎቹ ላይ ጥቃት በመሰንዘር ድል አደረጓቸው። እሱም ከደማስቆ በስተ ሰሜን እስከምትገኘው እስከ ሆባ ድረስ አሳደዳቸው። 16 የወሰዷቸውን ንብረቶችም ሁሉ አስመለሰ፤ በተጨማሪም ዘመዱን ሎጥንና ንብረቶቹን እንዲሁም ሴቶቹንና ሌሎቹን ሰዎች አስመለሰ።

17 አብራም ኮሎዶጎምርንና ከእሱ ጋር የነበሩትን ነገሥታት ድል አድርጎ ከተመለሰ በኋላ የሰዶም ንጉሥ ከአብራም ጋር ለመገናኘት ወደ ሻዌ ሸለቆ* ማለትም ወደ ንጉሡ ሸለቆ+ ወጣ። 18 የሳሌም ንጉሥ+ መልከጼዴቅም+ ምግብና የወይን ጠጅ ይዞ ወጣ፤ እሱም የልዑሉ አምላክ ካህን+ ነበር።

19 አብራምንም ባረከው፤ እንዲህም አለው፦

“ሰማይንና ምድርን የሠራው

ልዑሉ አምላክ አብራምን ይባርክ፤

20 የሚጨቁኑህን በእጅህ አሳልፎ የሰጠህ፣

ልዑሉ አምላክ ይወደስ!”

አብራምም ከሁሉም ነገር ላይ አንድ አሥረኛውን ሰጠው።+

21 ከዚያም የሰዶም ንጉሥ አብራምን “ሰዎቹን* ስጠኝ፤ ንብረቶቹን ግን ለራስህ ውሰድ” አለው። 22 አብራም ግን የሰዶምን ንጉሥ እንዲህ አለው፦ “ሰማይንና ምድርን ወደሠራው ወደ ልዑሉ አምላክ ወደ ይሖዋ እጄን አንስቼ እምላለሁ፣ 23 ‘አብራምን አበለጸግኩት’ እንዳትል የአንተ ከሆነው ነገር ምንም አልወስድም፤ ሌላው ቀርቶ ብጣሽ ክርም ሆነ የጫማ ማሰሪያ አልወስድም። 24 ወጣቶቹ ከበሉት ምግብ በስተቀር ምንም ነገር አልወስድም። ከእኔ ጋር የዘመቱት አኔር፣ ኤሽኮልና ማምሬ+ ግን ድርሻቸውን ይውሰዱ።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ