የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 20
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • አቢሜሌክ ሣራን ለአብርሃም መለሰለት (1-18)

ዘፍጥረት 20:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እንደ ባዕድ አገር ሰው ሆኖ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 13:18
  • +ዘኁ 13:26
  • +ዘፍ 25:17, 18
  • +ዘፍ 10:19፤ 26:6

ዘፍጥረት 20:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:11-13፤ 20:11, 12
  • +ዘፍ 12:15

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    5/15/2015፣ ገጽ 12

ዘፍጥረት 20:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:17፤ መዝ 105:14
  • +ዘዳ 22:22

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    7/15/1995፣ ገጽ 12

ዘፍጥረት 20:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ከእሷ ጋር የፆታ ግንኙነት አለመፈጸሙን ያመለክታል።

  • *

    ወይም “ጻድቅ የሆነን።”

ዘፍጥረት 20:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 105:14, 15
  • +ኢዮብ 42:8

ዘፍጥረት 20:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:18, 19፤ 26:9, 10

ዘፍጥረት 20:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:11, 12፤ 26:7

ዘፍጥረት 20:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 11:29

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)፣

    ቁጥር 3 2017፣ ገጽ 12

    ማመራመር፣ ገጽ 252-253

ዘፍጥረት 20:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:1
  • +ዘፍ 12:13

ዘፍጥረት 20:16

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “እነሆ፣ ይህ ለአንቺ የዓይን መሸፈኛ ነው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 20:2, 12

ዘፍጥረት 20:18

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በአቢሜሌክ ቤት ያለውን ማህፀን ሁሉ ፈጽሞ ዘግቶ ነበር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:17

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 20:1ዘፍ 13:18
ዘፍ. 20:1ዘኁ 13:26
ዘፍ. 20:1ዘፍ 25:17, 18
ዘፍ. 20:1ዘፍ 10:19፤ 26:6
ዘፍ. 20:2ዘፍ 12:11-13፤ 20:11, 12
ዘፍ. 20:2ዘፍ 12:15
ዘፍ. 20:3ዘፍ 12:17፤ መዝ 105:14
ዘፍ. 20:3ዘዳ 22:22
ዘፍ. 20:7መዝ 105:14, 15
ዘፍ. 20:7ኢዮብ 42:8
ዘፍ. 20:10ዘፍ 12:18, 19፤ 26:9, 10
ዘፍ. 20:11ዘፍ 12:11, 12፤ 26:7
ዘፍ. 20:12ዘፍ 11:29
ዘፍ. 20:13ዘፍ 12:1
ዘፍ. 20:13ዘፍ 12:13
ዘፍ. 20:16ዘፍ 20:2, 12
ዘፍ. 20:18ዘፍ 12:17
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 20:1-18

ዘፍጥረት

20 አብርሃም ድንኳኑን+ ከዚያ ነቅሎ ወደ ኔጌብ ምድር ሄደ፤ በቃዴስና+ በሹር+ መካከልም መኖር ጀመረ። በጌራራ+ እየኖረ* ሳለ 2 በድጋሚ ሚስቱን ሣራን “እህቴ ናት” አለ።+ በመሆኑም የጌራራ ንጉሥ አቢሜሌክ ሰዎችን ልኮ ሣራን አስመጣት፤ ከዚያም ወሰዳት።+ 3 ከዚያም አምላክ ለአቢሜሌክ ሌሊት በሕልም ተገልጦለት “በወሰድካት ሴት የተነሳ ትሞታለህ፤+ ምክንያቱም እሷ ያገባችና ባለቤት ያላት ሴት ናት”+ አለው። 4 ሆኖም አቢሜሌክ ወደ እሷ አልቀረበም ነበር።* በመሆኑም እንዲህ አለ፦ “ይሖዋ፣ ምንም በደል ያልፈጸመን* ብሔር ታጠፋለህ? 5 እሱ ‘እህቴ ናት’ አላለኝም? እሷስ ብትሆን ‘ወንድሜ ነው’ አላለችም? ይህን ያደረግኩት በቅን ልቦናና በንጹሕ እጅ ነው።” 6 ከዚያም እውነተኛው አምላክ በሕልም ተገልጦለት እንዲህ አለው፦ “ይህን ያደረግከው በቅን ልቦና ተነሳስተህ እንደሆነ አውቃለሁ፤ በእኔም ላይ ኃጢአት እንዳትሠራ ጠብቄሃለሁ። እንድትነካት ያልፈቀድኩልህም ለዚህ ነው። 7 በል አሁን የሰውየውን ሚስት መልስ፤ እሱ ነቢይ ነውና፤+ ስለ አንተም ልመና ያቀርባል፤+ አንተም በሕይወት ትኖራለህ። እሷን ባትመልስ ግን በእርግጥ እንደምትሞት እወቅ፤ አንተም ሆንክ የአንተ የሆነው ሁሉ ትሞታላችሁ።”

8 አቢሜሌክ በማለዳ ተነሳ፤ አገልጋዮቹንም በሙሉ ጠርቶ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፤ እነሱም በጣም ፈሩ። 9 ከዚያም አቢሜሌክ አብርሃምን ጠርቶ እንዲህ አለው፦ “ይህ ያደረግክብን ነገር ምንድን ነው? በእኔም ሆነ በግዛቴ ላይ እንዲህ ያለውን ታላቅ ኃጢአት ያመጣህብን ለመሆኑ ምን በድዬህ ነው? ያደረግክብኝ ነገር ትክክል አይደለም።” 10 በመቀጠልም አቢሜሌክ አብርሃምን “ለመሆኑ ይህን ያደረግከው ምን አስበህ ነው?” አለው።+ 11 አብርሃምም እንዲህ አለው፦ “ይህን ያደረግኩት ‘በዚህ ስፍራ እንደሆነ ፈሪሃ አምላክ የሚባል ነገር የለም፤ ሰዎቹ ለሚስቴ ሲሉ ሊገድሉኝ ይችላሉ’ ብዬ ስለሰጋሁ ነው።+ 12 ደግሞም እኮ በእርግጥ እህቴ ናት፤ የእናቴ ልጅ ባትሆንም የአባቴ ልጅ ናት፤ እሷም ሚስቴ ሆነች።+ 13 በመሆኑም አምላክ ከአባቴ ቤት ወጥቼ ከአገር አገር እየዞርኩ እንድኖር በነገረኝ ጊዜ+ ‘በምንሄድበት ስፍራ ሁሉ “ወንድሜ ነው” ብለሽ በመናገር ታማኝ ፍቅር አሳዪኝ’ ብያት ነበር።”+

14 ከዚያም አቢሜሌክ በጎችን፣ ከብቶችን እንዲሁም ወንድና ሴት አገልጋዮችን ለአብርሃም ሰጠው፤ ሚስቱን ሣራንም መለሰለት። 15 በተጨማሪም አቢሜሌክ “አገሬ አገርህ ናት፤ ደስ ባለህ ቦታ መኖር ትችላለህ” አለው። 16 ሣራንም እንዲህ አላት፦ “ይኸው ለወንድምሽ+ 1,000 የብር ሰቅል እሰጠዋለሁ። ይህም አንቺ ንጹሕ ሰው መሆንሽን ከአንቺ ጋር ባሉት ሰዎች ሁሉ ፊትም ሆነ በሌሎች ሰዎች ፊት የሚያሳውቅ ምልክት ነው፤* አንቺም ከማንኛውም ነቀፋ ነፃ ነሽ።” 17 አብርሃምም ወደ እውነተኛው አምላክ ልመና አቀረበ፤ አምላክም አቢሜሌክን፣ ሚስቱንና ሴት ባሪያዎቹን ፈወሳቸው፤ እነሱም ልጆች መውለድ ጀመሩ፤ 18 ምክንያቱም ይሖዋ በአብርሃም ሚስት በሣራ የተነሳ በአቢሜሌክ ቤት ያሉትን ሴቶች ሁሉ መሃን አድርጎ ነበር።*+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ