የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መዝሙር 107
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

መዝሙር የመጽሐፉ ይዘት

      • አስደናቂ ለሆኑት ሥራዎቹ አምላክን አመስግኑ

        • “በትክክለኛው መንገድ መራቸው” (7)

        • የተጠማውንና የተራበውን አርክቷል (9)

        • ‘ከጨለማ አወጣቸው’ (14)

        • ቃሉን ልኮ ፈወሳቸው (20)

        • ‘ድሆችን ከጭቆና ይጠብቃል’ (41)

መዝሙር 107:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሉቃስ 18:19
  • +1ዜና 16:34፤ መዝ 103:17

መዝሙር 107:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ይሖዋ የተቤዣቸው።”

  • *

    ወይም “ኃይል።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 35:10፤ ኤር 15:21፤ ሚክ 4:10

መዝሙር 107:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከፀሐይ መውጫና ከፀሐይ መግቢያ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 106:47፤ ኢሳ 43:5, 6፤ ኤር 29:14፤ 31:8

መዝሙር 107:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳቸው ተዝለፈለፈች።”

መዝሙር 107:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሆሴዕ 5:14, 15
  • +ኢሳ 41:17

መዝሙር 107:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ነህ 11:3
  • +ኢሳ 30:21

መዝሙር 107:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 40:5
  • +1ዜና 16:8

መዝሙር 107:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የተጠማችውን ነፍስ።”

  • *

    ወይም “የተራበችውንም ነፍስ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 34:10፤ ኢሳ 55:2፤ ሉቃስ 1:53

መዝሙር 107:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 106:43፤ ሰቆ 3:42

መዝሙር 107:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 26:21

መዝሙር 107:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 68:6፤ 146:7፤ ኢሳ 49:8, 9፤ 61:1

መዝሙር 107:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሰቆ 3:22

መዝሙር 107:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 45:1, 2

መዝሙር 107:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሰቆ 3:39
  • +ኤር 2:19

መዝሙር 107:18

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳቸው ማንኛውንም ምግብ ተጸየፈች።”

መዝሙር 107:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 147:3

መዝሙር 107:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 7:12፤ መዝ 50:14

መዝሙር 107:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 9:21፤ ሕዝ 27:9

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    10/15/2005፣ ገጽ 32

መዝሙር 107:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 1:21፤ መዝ 104:25

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    10/15/2005፣ ገጽ 32

መዝሙር 107:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 135:7፤ ኤር 10:13፤ ዮናስ 1:4

መዝሙር 107:26

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳቸው ቀለጠች።”

መዝሙር 107:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዮናስ 1:4, 13

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    9/1/2006፣ ገጽ 14

መዝሙር 107:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዮናስ 1:14

መዝሙር 107:29

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 65:7፤ 89:9፤ ዮናስ 1:15

መዝሙር 107:31

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 105:5

መዝሙር 107:32

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “መቀመጫ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 111:1

መዝሙር 107:33

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 17:1, 7፤ ኢሳ 42:15፤ አሞጽ 4:7

መዝሙር 107:34

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 13:10፤ ዘዳ 29:22, 23

መዝሙር 107:35

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 3:17፤ ኢሳ 35:7፤ 41:18

መዝሙር 107:36

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 107:7
  • +መዝ 146:7፤ ሉቃስ 1:53

መዝሙር 107:37

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 65:21
  • +ሥራ 14:17

መዝሙር 107:38

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 7:13, 14

መዝሙር 107:40

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢዮብ 12:21, 24

መዝሙር 107:41

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከፍ ያለ ቦታ ላይ ያስቀምጣቸዋል።” የማይደረስበት ቦታ ላይ ያደርጋቸዋል ማለት ነው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 2:8

መዝሙር 107:42

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 58:10
  • +ዘፀ 11:7፤ መዝ 63:11

መዝሙር 107:43

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 64:9፤ ሆሴዕ 14:9
  • +መዝ 77:12፤ 143:5፤ ኤር 9:24

ተዛማጅ ሐሳብ

መዝ. 107:1ሉቃስ 18:19
መዝ. 107:11ዜና 16:34፤ መዝ 103:17
መዝ. 107:2ኢሳ 35:10፤ ኤር 15:21፤ ሚክ 4:10
መዝ. 107:3መዝ 106:47፤ ኢሳ 43:5, 6፤ ኤር 29:14፤ 31:8
መዝ. 107:6ሆሴዕ 5:14, 15
መዝ. 107:6ኢሳ 41:17
መዝ. 107:7ነህ 11:3
መዝ. 107:7ኢሳ 30:21
መዝ. 107:8መዝ 40:5
መዝ. 107:81ዜና 16:8
መዝ. 107:9መዝ 34:10፤ ኢሳ 55:2፤ ሉቃስ 1:53
መዝ. 107:11መዝ 106:43፤ ሰቆ 3:42
መዝ. 107:12ዘሌ 26:21
መዝ. 107:14መዝ 68:6፤ 146:7፤ ኢሳ 49:8, 9፤ 61:1
መዝ. 107:15ሰቆ 3:22
መዝ. 107:16ኢሳ 45:1, 2
መዝ. 107:17ሰቆ 3:39
መዝ. 107:17ኤር 2:19
መዝ. 107:20መዝ 147:3
መዝ. 107:22ዘሌ 7:12፤ መዝ 50:14
መዝ. 107:232ዜና 9:21፤ ሕዝ 27:9
መዝ. 107:24ዘፍ 1:21፤ መዝ 104:25
መዝ. 107:25መዝ 135:7፤ ኤር 10:13፤ ዮናስ 1:4
መዝ. 107:27ዮናስ 1:4, 13
መዝ. 107:28ዮናስ 1:14
መዝ. 107:29መዝ 65:7፤ 89:9፤ ዮናስ 1:15
መዝ. 107:31መዝ 105:5
መዝ. 107:32መዝ 111:1
መዝ. 107:331ነገ 17:1, 7፤ ኢሳ 42:15፤ አሞጽ 4:7
መዝ. 107:34ዘፍ 13:10፤ ዘዳ 29:22, 23
መዝ. 107:352ነገ 3:17፤ ኢሳ 35:7፤ 41:18
መዝ. 107:36መዝ 107:7
መዝ. 107:36መዝ 146:7፤ ሉቃስ 1:53
መዝ. 107:37ኢሳ 65:21
መዝ. 107:37ሥራ 14:17
መዝ. 107:38ዘዳ 7:13, 14
መዝ. 107:40ኢዮብ 12:21, 24
መዝ. 107:411ሳሙ 2:8
መዝ. 107:42መዝ 58:10
መዝ. 107:42ዘፀ 11:7፤ መዝ 63:11
መዝ. 107:43መዝ 64:9፤ ሆሴዕ 14:9
መዝ. 107:43መዝ 77:12፤ 143:5፤ ኤር 9:24
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
  • 35
  • 36
  • 37
  • 38
  • 39
  • 40
  • 41
  • 42
  • 43
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
መዝሙር 107:1-43

መዝሙር

አምስተኛ መጽሐፍ

(መዝሙር 107-150)

107 ይሖዋ ጥሩ+ ስለሆነ ምስጋና አቅርቡለት፤

ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።+

 2 ይሖዋ የዋጃቸው፣*

አዎ፣ ከጠላት እጅ* የዋጃቸው+ ይህን ይበሉ፤

 3 ከምሥራቅና ከምዕራብ፣*

ከሰሜንና ከደቡብ፣

ከየአገሩ አንድ ላይ የሰበሰባቸው+ ይህን ይናገሩ።

 4 በምድረ በዳ፣ በበረሃም ተቅበዘበዙ፤

ሊኖሩ ወደሚችሉበት ከተማ የሚወስድ መንገድ አላገኙም።

 5 ተርበውና ተጠምተው ነበር፤

ኃይላቸው ከመሟጠጡ የተነሳ ተዝለፈለፉ።*

 6 በተጨነቁ ጊዜ ወደ ይሖዋ ይጮኹ ነበር፤+

እሱም ከደረሰባቸው መከራ ታደጋቸው።+

 7 መኖር ወደሚችሉበት ከተማ እንዲደርሱ+

በትክክለኛው መንገድ መራቸው።+

 8 ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩና

ለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች+ ይሖዋን ያመስግኑት።+

 9 እሱ የተጠማውን* አርክቷልና፤

የተራበውንም* በመልካም ነገሮች አጥግቧል።+

10 አንዳንዶች በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የሚኖሩ፣

በመከራ ውስጥ ያሉና በሰንሰለት የተጠፈሩ እስረኞች ነበሩ።

11 በአምላክ ቃል ላይ ዓምፀዋልና፤

የልዑሉን አምላክ ምክር ንቀዋል።+

12 ስለዚህ በደረሰባቸው መከራ ልባቸው እንዲለሰልስ አደረገ፤+

ተሰናከሉ፤ የሚረዳቸውም አንዳች ሰው አልነበረም።

13 በተጨነቁ ጊዜ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ተጣሩ፤

እሱም ከደረሰባቸው መከራ አዳናቸው።

14 ከድቅድቅ ጨለማ አወጣቸው፤

የታሰሩበትንም ሰንሰለት በጠሰ።+

15 ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩና

ለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት።+

16 እሱ የመዳብ በሮችን ሰብሯልና፤

የብረት መወርወሪያዎችንም ቆርጧል።+

17 ከጥፋታቸውና ከበደላቸው የተነሳ+

ሞኝ ሆኑ፤ ለመከራም ተዳረጉ።+

18 የምግብ ፍላጎታቸው ሙሉ በሙሉ ጠፋ፤*

ወደ ሞት ደጆች ቀረቡ።

19 በተጨነቁ ጊዜ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ይጣሩ ነበር፤

እሱም ከደረሰባቸው መከራ ያድናቸው ነበር።

20 ቃሉን ልኮ ይፈውሳቸው፣+

ከተያዙበትም ጉድጓድ ይታደጋቸው ነበር።

21 ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩና

ለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት።

22 የምስጋና መሥዋዕት ያቅርቡ፤+

በእልልታም ሥራዎቹን ያስታውቁ።

23 በባሕር ላይ በመርከቦች የሚጓዙ፣

በሰፋፊ ውኃዎች ላይ ንግድ የሚያካሂዱ፣+

24 እነሱ የይሖዋን ሥራዎች፣

በጥልቁም ውስጥ ያከናወናቸውን አስደናቂ ነገሮች+ ተመልክተዋል፤

25 እሱ በቃሉ አውሎ ነፋስ ሲያስነሳ፣+

የባሕሩንም ማዕበል ሲያናውጥ አይተዋል።

26 ወደ ሰማይ ይወጣሉ፣

ወደ ጥልቆችም ይወርዳሉ።

እየመጣባቸው ካለው መከራ የተነሳ ሐሞታቸው ፈሰሰ።*

27 እንደሰከረ ሰው ይንገዳገዳሉ፤ ደግሞም ይወላገዳሉ፤

ችሎታቸውም ሁሉ የፈየደላቸው ነገር የለም።+

28 በዚህ ጊዜ ከጭንቀታቸው የተነሳ ወደ ይሖዋ ይጮኻሉ፤+

እሱም ከደረሰባቸው መከራ ይታደጋቸዋል።

29 አውሎ ነፋሱ እንዲቆም ያደርጋል፤

የባሕሩም ሞገዶች ጸጥ ይላሉ።+

30 ሞገዶቹ ጸጥ ሲሉ ሰዎቹ ሐሴት ያደርጋሉ፤

እሱም ወዳሰቡት ወደብ ይመራቸዋል።

31 ሕዝቦች ስለ ታማኝ ፍቅሩና

ለሰው ልጆች ስላደረጋቸው አስደናቂ ሥራዎች ይሖዋን ያመስግኑት።+

32 በሕዝብ ጉባኤ መካከል ከፍ ከፍ ያድርጉት፤+

በሽማግሌዎችም ሸንጎ* ያወድሱት።

33 እሱ ወንዞችን ወደ በረሃ፣

የውኃ ምንጮችንም ወደ ደረቅ መሬት ይለውጣል፤+

34 ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሳ

ፍሬያማዋን አገር ጨዋማ የሆነ ጠፍ ምድር ያደርጋታል።+

35 በረሃውን ቄጠማ የሞላበት ኩሬ፣

ደረቁንም ምድር የውኃ ምንጭ ያደርጋል።+

36 ሊኖሩ የሚችሉበትን ከተማ እንዲመሠርቱ፣+

የተራቡ ሰዎችን በዚያ ያኖራል።+

37 መሬት ላይ ዘሩ፤ ወይንም ተከሉ፤+

መሬቱም ብዙ ምርት ሰጠ።+

38 እሱ ይባርካቸዋል፤ እነሱም እጅግ ይበዛሉ፤

የከብቶቻቸው ብዛት እንዲያንስ አያደርግም።+

39 ሆኖም ከደረሰባቸው ጭቆና፣ መከራና ሐዘን የተነሳ

ዳግመኛ ቁጥራቸው ተመናመነ፤ ተዋረዱም።

40 በታላላቅ ሰዎች ላይ የውርደት መዓት ያዘንባል፤

መንገድ በሌለበት ጠፍ መሬትም እንዲቅበዘበዙ ያደርጋል።+

41 ድሆችን ግን ከጭቆና ይጠብቃል፤*+

ቤተሰባቸውንም እንደ መንጋ ያበዛል።

42 ቅኖች ይህን አይተው ሐሴት ያደርጋሉ፤+

ዓመፀኞች ሁሉ ግን አፋቸውን ይዘጋሉ።+

43 ጥበበኛ የሆነ ሁሉ እነዚህን ነገሮች ልብ ይላል፤+

ደግሞም ይሖዋ በታማኝ ፍቅር ያከናወናቸውን ነገሮች በትኩረት ይመለከታል።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ