የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 25:8
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  8 ሞትን ለዘላለም ይውጣል፤*+

      ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ከፊት ሁሉ እንባን ያብሳል።*+

      በሕዝቡ ላይ የደረሰውን ነቀፋ ከመላው ምድር ያስወግዳል፤

      ይሖዋ ራሱ ይህን ተናግሯልና።

  • ሆሴዕ 13:14
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 14 ከመቃብር* እጅ እዋጃቸዋለሁ፤

      ከሞትም እታደጋቸዋለሁ።+

      ሞት ሆይ፣ መንደፊያህ የት አለ?+

      መቃብር ሆይ፣ አጥፊነትህ የት አለ?+

      ርኅራኄ ከዓይኔ ፊት ይሰወራል።

  • ማርቆስ 12:26
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 26 ስለ ሙታን መነሳት ግን በሙሴ መጽሐፍ፣ ስለ ቁጥቋጦው በሚገልጸው ታሪክ ላይ አምላክ ሙሴን ‘እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክና የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ እንዳለው አላነበባችሁም?+

  • ዮሐንስ 5:28, 29
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 28 በዚህ አትደነቁ፤ በመታሰቢያ መቃብር ያሉ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣልና፤+ 29 መልካም የሠሩ ለሕይወት ትንሣኤ፣ ክፉ የሠሩ* ደግሞ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉ።+

  • ዮሐንስ 11:24, 25
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 24 ማርታም “በመጨረሻው ቀን በትንሣኤ እንደሚነሳ አውቃለሁ” አለችው።+ 25 ኢየሱስም እንዲህ አላት፦ “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ።+ በእኔ የሚያምን* ሁሉ ቢሞት እንኳ እንደገና ሕያው ይሆናል፤

  • የሐዋርያት ሥራ 24:15
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 15 ደግሞም እነዚህ ሰዎች ራሳቸው ተስፋ እንደሚያደርጉት ጻድቃንም ሆኑ ጻድቃን ያልሆኑ ሰዎች+ ከሞት እንደሚነሱ+ በአምላክ ተስፋ አለኝ።

  • 1 ቆሮንቶስ 15:21
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 21 ሞት የመጣው በአንድ ሰው በኩል+ ስለሆነ የሙታን ትንሣኤም በአንድ ሰው በኩል ነው።+

  • 1 ተሰሎንቄ 4:14
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 14 ኢየሱስ እንደሞተና ከሞት እንደተነሳ የምናምን ከሆነ+ ከኢየሱስ ጋር አንድነት ኖሯቸው በሞት ያንቀላፉትንም አምላክ ሕይወት ሰጥቶ ከእሱ ጋር እንዲሆኑ ያደርጋል።+

  • ራእይ 20:12, 13
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 12 ከዚያም ሙታንን፣ ታላላቆችንና ታናናሾችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ፤ የመጽሐፍ ጥቅልሎችም ተከፈቱ። ሌላም ጥቅልል ተከፈተ፤ ይህም የሕይወት መጽሐፍ ጥቅልል ነው።+ ሙታን በጥቅልሎቹ ውስጥ በተጻፉት ነገሮች መሠረት እንደየሥራቸው ፍርድ ተሰጣቸው።+ 13 ባሕርም በውስጡ ያሉትን ሙታን ሰጠ፤ ሞትና መቃብርም* በውስጣቸው ያሉትን ሙታን ሰጡ፤ እነሱም እያንዳንዳቸው እንደየሥራቸው ፍርድ ተሰጣቸው።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ